የማርቆስ ወንጌል ም.፲
21: ኢየሱስም ወደ እርሱ ተመልክቶ ወደደውና እንዲህ አለው፦ “አንድ ነገር ጐደለህ፤ ሂድ፥ ያለህን ሁሉ ሽጠህ ለድሆች ስጥ፥ በሰማይም መዝገብ ታገኛለህ፥ መስቀሉንም ተሸክመህ፡ ና፥ ተከተለኝ።”
22: ነገር ግን ስለዚህ ነገር ፊቱ ጠቈረ፥ ብዙ ንብረት ነበረውና እያዘነም ሄደ።
23: ኢየሱስም ዘወር ብሎ አይቶ ደቀ መዛሙርቱን፦ “ገንዘብ ላላቸው ወደ እግዚአብሔር መንግሥት መግባት እንዴት ጭንቅ ይሆናል፡” አላቸው።
24: ደቀ መዛሙርቱም እነዚህን ቃሎች አደነቁ። ኢየሱስም ደግሞ መልሶ፦ “ልጆች ሆይ፥ በገንዘብ ለሚታመኑ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት መግባት እንዴት ጭንቅ ነው።
25: ባለ ጠጋ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ከሚገባ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ቢያልፍ ይቀላል፡” አላቸው።
26: እነርሱም ያለ መጠን ተገረሙና እርስ በርሳቸው፦ “እንግዲያ ማን ሊድን ይችላል?” ተባባሉ።
27: ኢየሱስም ተመለከታቸውና፦ “ይህ በእግዚአብሔር ዘንድ እንጂ በሰው ዘንድ አይቻልም፤ በእግዚአብሔር ዘንድ ሁሉ ይቻላልና፡” አለ።
28: ጴጥሮስም፦ “እነሆ፥ እኛ ሁሉን ትተን ተከተልንህ፡” ይለው ጀመር።
29: ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለ፦ “እውነት እላችኋለሁ፥ ስለ እኔና ስለ ወንጌል ቤትን ወይም ወንድሞችን ወይም እኅቶችን ወይም አባትን ወይም እናትን ወይም ሚስትን ወይም ልጆችን ወይም እርሻን የተወ፤
30: አሁን በዚህ ዘመን ከስደት ጋር ቤቶችን ወንድሞችንና እኅቶችንም እናቶችንም ልጆችንም እርሻንም መቶ እጥፍ፥ በሚመጣውም ዓለም የዘላለም ሕይወት የማይቀበል ማንም የለም።
31: ግን ብዙ ፊተኞች ኋለኞች ኋለኞችም ፊተኞች ይሆናሉ።”
21: ኢየሱስም ወደ እርሱ ተመልክቶ ወደደውና እንዲህ አለው፦ “አንድ ነገር ጐደለህ፤ ሂድ፥ ያለህን ሁሉ ሽጠህ ለድሆች ስጥ፥ በሰማይም መዝገብ ታገኛለህ፥ መስቀሉንም ተሸክመህ፡ ና፥ ተከተለኝ።”
22: ነገር ግን ስለዚህ ነገር ፊቱ ጠቈረ፥ ብዙ ንብረት ነበረውና እያዘነም ሄደ።
23: ኢየሱስም ዘወር ብሎ አይቶ ደቀ መዛሙርቱን፦ “ገንዘብ ላላቸው ወደ እግዚአብሔር መንግሥት መግባት እንዴት ጭንቅ ይሆናል፡” አላቸው።
24: ደቀ መዛሙርቱም እነዚህን ቃሎች አደነቁ። ኢየሱስም ደግሞ መልሶ፦ “ልጆች ሆይ፥ በገንዘብ ለሚታመኑ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት መግባት እንዴት ጭንቅ ነው።
25: ባለ ጠጋ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ከሚገባ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ቢያልፍ ይቀላል፡” አላቸው።
26: እነርሱም ያለ መጠን ተገረሙና እርስ በርሳቸው፦ “እንግዲያ ማን ሊድን ይችላል?” ተባባሉ።
27: ኢየሱስም ተመለከታቸውና፦ “ይህ በእግዚአብሔር ዘንድ እንጂ በሰው ዘንድ አይቻልም፤ በእግዚአብሔር ዘንድ ሁሉ ይቻላልና፡” አለ።
28: ጴጥሮስም፦ “እነሆ፥ እኛ ሁሉን ትተን ተከተልንህ፡” ይለው ጀመር።
29: ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለ፦ “እውነት እላችኋለሁ፥ ስለ እኔና ስለ ወንጌል ቤትን ወይም ወንድሞችን ወይም እኅቶችን ወይም አባትን ወይም እናትን ወይም ሚስትን ወይም ልጆችን ወይም እርሻን የተወ፤
30: አሁን በዚህ ዘመን ከስደት ጋር ቤቶችን ወንድሞችንና እኅቶችንም እናቶችንም ልጆችንም እርሻንም መቶ እጥፍ፥ በሚመጣውም ዓለም የዘላለም ሕይወት የማይቀበል ማንም የለም።
31: ግን ብዙ ፊተኞች ኋለኞች ኋለኞችም ፊተኞች ይሆናሉ።”