Forward from: በእንተ ቅዱሳን ኅሩያን (ከገድላት አንደበት)
የየትኛውም ብሔር ተወላጅ ብትኾን መጀመሪያ በራስህ፤ ቀጥሎ በቤተሰብህ፤ ከዚያም በቅድስት ቤተ ክርስቲያንህ እና በመጨረሻም በሀገር ላይ ይመጣ ያለውን አስከፊ እልቂትና መከራ ሳይታክቱ ሌት ተቀን ነግረውሃልና እነዚኽ ኹለት ሰዎች የኢትዮጵያ ሕዝብ ባለ ዕዳዎች ናቸው። ግለሰቦቹን ወደድካቸውም ጠላኻቸውም፤ ሰማኻቸውም አልሰማኻቸውም እርሱ ለቤተ ክርስቲያንና ለሀገር ነቢይም ሐዋርያም መምህርም ኾነው ትናንትም ዛሬም ሲጮኹ አይተንና ሰምተን እንደ እብድ ብንቈጥራቸውም ነገ ጅብ ከሔደ በኋላ የውሻ ጩኸት የምንጮኸው እኛ ነን። ይኽ በእርግጥ ሩቅ አይደለም። የዐዋጅ ነጋሪ ቃል ሲጮህ አልሰማ ብለህ ለንስሓ ያልተዘጋጀህ ኹላ አይዞህ ጊዜው ሩቅ አይደለም። አራጁ ቢላውን ስሎ ሞርዶ ከደጅ ቆሞልሃል፤ አንተም አንገትህን አደንድነህ ጠብቀው።