...ንዑሳን ንባባት ከሚለው የቀጠለ...
2,ማጥበቅ
ከንዑሳን ንባባት መካከል ሁለተኛው ንዑስ ንባብ ማጥበቅ ይባላል፡፡
ይህ የንባብ አይነት በግሱ መካከል የሚገኙትን ቃላት ጠበቅ አድርገን የምናነብበት የንባብ ዓይነት ነው።
# ጠብቀው የሚነበቡ ግሶች ምሳሌ ፡-
ግስ = ትርጉም = የሚጠብቀው ፊደል
ቀደሰ = አመሰገነ = "ደ" ጠብቆ ይነበባል
ዘመረ = ዘመረ = "መ" ጠብቆ ይነበባል
ነጸረ = ዓየ = "ጸ" ጠብቆ ይነበባል
ፈነወ = ላከ = "ነ" ጠብቆ ይነበባል
ለበወ = ልበኛ ሆነ = "በ" ጠብቆ ይነበባል
ሐወጸ = ጎበኘ = "ወ" ጠብቆ ይነበባል
መ'ነ'ነ = ናቀ = "ነ" ጠብቆ ይነበባል
ወደሰ = አመሰገነ = "ደ" ጠብቆ ይነበባል
ተዘከረ = አሰበ = "ከ" ጠብቆ ይነበባል
ተዐገሠ=ትዕግስተኛ ሆነ="ገ" ጠብቆ ይነበባል
ጸውዐ = ጠራ = "ው" ጠብቆ ይነበባል
ጸለየ = ለመነ = "ለ" ጠብቆ ይነበባል
ከላይ ያየናቸውን የመመሳሰሉት ሁሉ ጠብቀው ይነበባቡ በተለይ የቀደሰ ቤት ግሶች ለሚጠብቁት እንደ ማስረጃ ሊሆኑ ይችላሉ።
3,ማላላት
ከንዑሳን ንባባት መካከል ሦስተኛው ንዑስ ንባብ ማላላት ይባላል፡፡
ይህ የንባብ አይነት በግሱ መካከል የሚገኙትን ቃላት ላላ አድርገን የምናነብበት መንገድ ሲሆን የማጥበቅ ተቃራኒ የሆነ የንባብ ዓይነት ነው።
# ላልተው የሚነበቡ ግሶች ምሳሌ ፡-
ግስ = ትርጉም = የሚላላ ፊደል
ቀተለ = ገደለ = "ተ" ላልቶ ይነበባል
ሰረቀ = ሰረቀ = "ረ" ላልቶ ይነበባል
ተለወ =ተከተለ = "ለ" ላልቶ ይነበባል
ፈቀደ = ፈቀደ = "ቀ" ላልቶ ይነበባል
ሐቀፈ= አቀፈ = "ቀ" ላልቶ ይነበባል
ነበረ =ተቀመጠ= "በ" ላልቶ ይነበባል
ወለደ= ወለደ = "ለ" ላልቶ ይነበባል
ወረደ= ወረደ = "ረ" ላልቶ ይነበባል
ወሀበ= ሰጠ = "ሀ" ላልቶ ይነበባል
ሰከበ = ተኛ = "ከ" ላልቶ ይነበባል
መጽአ= መጣ = "ጽ" ላልቶ ይነበባል
ፈተወ = ወደደ = "ተ" ላልቶ ይነበባል
ተከለ= ተከለ = "ከ" ላልቶ ይነበባል
ከላይ ያየናቸውን የመመሳሰሉት ሁሉ ላልተው ይነበባቡ በተለይ የቀተለ ቤት ግሶች ላልተው ለሚነበቡት እንደ ማስረጃ ሊሆኑ ይችላሉ።
#በግእዝ ቋንቋ ውስጥ አንድ ቃል ሲጠብቅና ሲላላ የተለያየ ትርጉም ሊኖረው ይችላል፡፡
ምሳሌ ፡ -
√ሰበከ ("ከ"ሲጠብቅ) ➜ አስተማርህ
√ ሰበከ ("ከ" ሲላላ) ➜ አስተማረ
√መካን ("ካ" ሲጠብቅ) ➜ የማትወልድ ሴት
√መካን ("ካ" ሲለላ) ➜ ቦታ
√አጥመቀ ("ቀ"ሲጠብቅ) ➜ አጠመቅህ
√አጥመቀ ("ቀ" ሲላላ) ➜ አጠመቀ ይላል
ማሳሰቢያ
ለአንባብያን በትኩረት እንድትከታተሉት እና ከቻላችሁ ባላችሁበት ቦታ በማስታወሻ ማለትም በኖት ቡክ ኮፒ እያደረጋችሁ እንድታነቡ በጥብቅ ማስገንዘብ እወዳለሁ
ሊቀ ማዕምራን መዓዛ ፈንታሁን
የባሶ ሊበን ወረዳ ቤተ ክህነት
የስብከተ ወንጌል ልፍል ኃላፊ
የጁቤ
2,ማጥበቅ
ከንዑሳን ንባባት መካከል ሁለተኛው ንዑስ ንባብ ማጥበቅ ይባላል፡፡
ይህ የንባብ አይነት በግሱ መካከል የሚገኙትን ቃላት ጠበቅ አድርገን የምናነብበት የንባብ ዓይነት ነው።
# ጠብቀው የሚነበቡ ግሶች ምሳሌ ፡-
ግስ = ትርጉም = የሚጠብቀው ፊደል
ቀደሰ = አመሰገነ = "ደ" ጠብቆ ይነበባል
ዘመረ = ዘመረ = "መ" ጠብቆ ይነበባል
ነጸረ = ዓየ = "ጸ" ጠብቆ ይነበባል
ፈነወ = ላከ = "ነ" ጠብቆ ይነበባል
ለበወ = ልበኛ ሆነ = "በ" ጠብቆ ይነበባል
ሐወጸ = ጎበኘ = "ወ" ጠብቆ ይነበባል
መ'ነ'ነ = ናቀ = "ነ" ጠብቆ ይነበባል
ወደሰ = አመሰገነ = "ደ" ጠብቆ ይነበባል
ተዘከረ = አሰበ = "ከ" ጠብቆ ይነበባል
ተዐገሠ=ትዕግስተኛ ሆነ="ገ" ጠብቆ ይነበባል
ጸውዐ = ጠራ = "ው" ጠብቆ ይነበባል
ጸለየ = ለመነ = "ለ" ጠብቆ ይነበባል
ከላይ ያየናቸውን የመመሳሰሉት ሁሉ ጠብቀው ይነበባቡ በተለይ የቀደሰ ቤት ግሶች ለሚጠብቁት እንደ ማስረጃ ሊሆኑ ይችላሉ።
3,ማላላት
ከንዑሳን ንባባት መካከል ሦስተኛው ንዑስ ንባብ ማላላት ይባላል፡፡
ይህ የንባብ አይነት በግሱ መካከል የሚገኙትን ቃላት ላላ አድርገን የምናነብበት መንገድ ሲሆን የማጥበቅ ተቃራኒ የሆነ የንባብ ዓይነት ነው።
# ላልተው የሚነበቡ ግሶች ምሳሌ ፡-
ግስ = ትርጉም = የሚላላ ፊደል
ቀተለ = ገደለ = "ተ" ላልቶ ይነበባል
ሰረቀ = ሰረቀ = "ረ" ላልቶ ይነበባል
ተለወ =ተከተለ = "ለ" ላልቶ ይነበባል
ፈቀደ = ፈቀደ = "ቀ" ላልቶ ይነበባል
ሐቀፈ= አቀፈ = "ቀ" ላልቶ ይነበባል
ነበረ =ተቀመጠ= "በ" ላልቶ ይነበባል
ወለደ= ወለደ = "ለ" ላልቶ ይነበባል
ወረደ= ወረደ = "ረ" ላልቶ ይነበባል
ወሀበ= ሰጠ = "ሀ" ላልቶ ይነበባል
ሰከበ = ተኛ = "ከ" ላልቶ ይነበባል
መጽአ= መጣ = "ጽ" ላልቶ ይነበባል
ፈተወ = ወደደ = "ተ" ላልቶ ይነበባል
ተከለ= ተከለ = "ከ" ላልቶ ይነበባል
ከላይ ያየናቸውን የመመሳሰሉት ሁሉ ላልተው ይነበባቡ በተለይ የቀተለ ቤት ግሶች ላልተው ለሚነበቡት እንደ ማስረጃ ሊሆኑ ይችላሉ።
#በግእዝ ቋንቋ ውስጥ አንድ ቃል ሲጠብቅና ሲላላ የተለያየ ትርጉም ሊኖረው ይችላል፡፡
ምሳሌ ፡ -
√ሰበከ ("ከ"ሲጠብቅ) ➜ አስተማርህ
√ ሰበከ ("ከ" ሲላላ) ➜ አስተማረ
√መካን ("ካ" ሲጠብቅ) ➜ የማትወልድ ሴት
√መካን ("ካ" ሲለላ) ➜ ቦታ
√አጥመቀ ("ቀ"ሲጠብቅ) ➜ አጠመቅህ
√አጥመቀ ("ቀ" ሲላላ) ➜ አጠመቀ ይላል
ማሳሰቢያ
ለአንባብያን በትኩረት እንድትከታተሉት እና ከቻላችሁ ባላችሁበት ቦታ በማስታወሻ ማለትም በኖት ቡክ ኮፒ እያደረጋችሁ እንድታነቡ በጥብቅ ማስገንዘብ እወዳለሁ
ሊቀ ማዕምራን መዓዛ ፈንታሁን
የባሶ ሊበን ወረዳ ቤተ ክህነት
የስብከተ ወንጌል ልፍል ኃላፊ
የጁቤ