ፈረንሳይ ሁለት ቁልፍ መገልገያዎችን በማስረከብ ከሴኔጋል ወታደራዊ ኃይሏን ማስዉጣት ጀመረች
ፈረንሳይ ከሴኔጋል ወታደራዊ ኃይሏን አርብ ዕለት ማስለቀቅ የጀመረች ሲሆን ሁለቱን ቁልፍ መገልገያዎችን ለምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር በማስረከብ በቀጣናዊ ስትራቴጂዋ ላይ ሰፊ ለውጥ አድርጋለች። በሴኔጋል የሚገኘው የፈረንሳይ ኤምባሲ በሰጠው መግለጫ አርብ ማርች 7 ቀን 2025 የፈረንሣይ ወገን በማርቻል እና ሴንት-ኤክሱፔሪ ወረዳ ውስጥ ያሉትን መገልገያዎች እና መኖሪያ ቤቶች ለሴኔጋል ወገን አስረክቧል ብሏል።
"በሀን ፓርክ አቅራቢያ የሚገኙት እነዚህ ወረዳዎች ከ2024 ክረምት ጀምሮ ወደ ሴኔጋል ለመመለስ ዝግጁ ነበሩ።" ይህ እርምጃ ላይ የተደረሰው የሴኔጋል ፕሬዝዳንት ባሲሩ ዲዮማዬ ፋዬ የውጭ ኃይሎችን ከአገሪቱ ለማስወጣት ያደረጉትን ግፊት ተከትሎ በምዕራብ አፍሪካ ፈረንሳይ መገኘቱን የሚቃወሙ ሰፊ ዘመቻ መከፈተን ያሳያል። የፈረንሳይ በአካባቢው ያለው ተጽእኖ ቀስ በቀስ እየቀነሰ መጥቷል።
በአካባቢው ሀገራት እየጨመረ በመጣው ተቃውሞ የተነሳ ፈረንሳይ ጦሯን ከቡርኪናፋሶ፣ ኒጀር እና ቻድን ለቀው መውጣታቸው ይታወሳል። የፈረንሳይን መውጣት ተከትሎ ባለፈው ወር የጋራ ኮሚሽን የተቋቋመ ሲሆን የፈረንሳይ ጦር በቅርቡ በዳካር የሚገኙ 162 የሴኔጋል ሰራተኞችን አሰናብቷል። የፈረንሳይ ኤምባሲ ግን በሴኔጋል ምን ያህል ወታደሮቹ እንደቀሩ አልገለጸም።
ፈረንሳይ የአፍሪካ ወታደራዊ አሻራዋን በከፍተኛ ደረጃ ለመቀነስ ማቀዷን ያስታወቀች ሲሆን፥ ጅቡቲ በአህጉሪቱ ብቸኛ የፈረንሳይ ቋሚ መቀመጫ ትሆናለች ተብሎ ይጠበቃል። ፓሪስ እንደገለጸችው የመከላከያ ስልጠና ወይም ወታደራዊ ድጋፍን ከዚህ በኃላ በሀገራት ጥያቄ መሰረት ብቻ ለማድረግ ውሳኔ አሳልፋለች።
በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል
ፈረንሳይ ከሴኔጋል ወታደራዊ ኃይሏን አርብ ዕለት ማስለቀቅ የጀመረች ሲሆን ሁለቱን ቁልፍ መገልገያዎችን ለምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር በማስረከብ በቀጣናዊ ስትራቴጂዋ ላይ ሰፊ ለውጥ አድርጋለች። በሴኔጋል የሚገኘው የፈረንሳይ ኤምባሲ በሰጠው መግለጫ አርብ ማርች 7 ቀን 2025 የፈረንሣይ ወገን በማርቻል እና ሴንት-ኤክሱፔሪ ወረዳ ውስጥ ያሉትን መገልገያዎች እና መኖሪያ ቤቶች ለሴኔጋል ወገን አስረክቧል ብሏል።
"በሀን ፓርክ አቅራቢያ የሚገኙት እነዚህ ወረዳዎች ከ2024 ክረምት ጀምሮ ወደ ሴኔጋል ለመመለስ ዝግጁ ነበሩ።" ይህ እርምጃ ላይ የተደረሰው የሴኔጋል ፕሬዝዳንት ባሲሩ ዲዮማዬ ፋዬ የውጭ ኃይሎችን ከአገሪቱ ለማስወጣት ያደረጉትን ግፊት ተከትሎ በምዕራብ አፍሪካ ፈረንሳይ መገኘቱን የሚቃወሙ ሰፊ ዘመቻ መከፈተን ያሳያል። የፈረንሳይ በአካባቢው ያለው ተጽእኖ ቀስ በቀስ እየቀነሰ መጥቷል።
በአካባቢው ሀገራት እየጨመረ በመጣው ተቃውሞ የተነሳ ፈረንሳይ ጦሯን ከቡርኪናፋሶ፣ ኒጀር እና ቻድን ለቀው መውጣታቸው ይታወሳል። የፈረንሳይን መውጣት ተከትሎ ባለፈው ወር የጋራ ኮሚሽን የተቋቋመ ሲሆን የፈረንሳይ ጦር በቅርቡ በዳካር የሚገኙ 162 የሴኔጋል ሰራተኞችን አሰናብቷል። የፈረንሳይ ኤምባሲ ግን በሴኔጋል ምን ያህል ወታደሮቹ እንደቀሩ አልገለጸም።
ፈረንሳይ የአፍሪካ ወታደራዊ አሻራዋን በከፍተኛ ደረጃ ለመቀነስ ማቀዷን ያስታወቀች ሲሆን፥ ጅቡቲ በአህጉሪቱ ብቸኛ የፈረንሳይ ቋሚ መቀመጫ ትሆናለች ተብሎ ይጠበቃል። ፓሪስ እንደገለጸችው የመከላከያ ስልጠና ወይም ወታደራዊ ድጋፍን ከዚህ በኃላ በሀገራት ጥያቄ መሰረት ብቻ ለማድረግ ውሳኔ አሳልፋለች።
በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል