የወረባቦ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪን ጨምሮ የወረዳዉ ፖሊስ ሃላፊዎች ተገደሉ
የወረባቦ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ፈንታው ከበደ፣ የወረባቦ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት የወንጀል ምርመራ ክፍል ኃላፊ እና ተወካይ የፖሊስ ጽ/ቤት ኃላፊ ዋና ኢንስፔክተር አድስ ዘመን ፍሰሃ እና ሹፌር አቶ ከበደ እንድሪስ ለመስክ ስራ በወጡበት በታጠቁ ፅንፈኛ ሃይሎች በደረሰባቸው ጥቃት ሕይወታቸው አልፏል ሲል የዞኑ መንግስት አሳዉቋል::
የዞኑ መንግስት "ፅንፈኛ ሀይሎች" ያላቸዉ አካላት ግድያዉን ፈጽመዋል ብሏል።
አመራሮቹ ለስራ በጉዞ ላይ ያሉ ባለሙያዎችን መንገድ ላይ በደፈጣ ጥቃት ጠብቀው ገድለዋል ሲል በመግለጫው መጥቀሱን ዳጉ ጆርናል ተመልክቷል።
የዞኑ መንግስት እነዚህ ህይወታቸውን ያጡ አመራርና ባለሙያ የህዝብና የመንግስትን ተልዕኮ ለማስፈፀም ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ህብረተሰቡን በልማት እና በመልካም አስተዳደር ተጠቃሚ ለማድረግ ቀን ከሌት ሲተጉ የነበሩ ቅንና ታታሪ የህዝብ ልጆች ነበሩ ብሏል።
የዞኑ መንግስት በግድያዉ ህይወታቸዉን ላጡ ቤተሰቦቻቸዉ እና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን ተመኝቷል።
#ዳጉ_ጆርናል
የወረባቦ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ፈንታው ከበደ፣ የወረባቦ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት የወንጀል ምርመራ ክፍል ኃላፊ እና ተወካይ የፖሊስ ጽ/ቤት ኃላፊ ዋና ኢንስፔክተር አድስ ዘመን ፍሰሃ እና ሹፌር አቶ ከበደ እንድሪስ ለመስክ ስራ በወጡበት በታጠቁ ፅንፈኛ ሃይሎች በደረሰባቸው ጥቃት ሕይወታቸው አልፏል ሲል የዞኑ መንግስት አሳዉቋል::
የዞኑ መንግስት "ፅንፈኛ ሀይሎች" ያላቸዉ አካላት ግድያዉን ፈጽመዋል ብሏል።
አመራሮቹ ለስራ በጉዞ ላይ ያሉ ባለሙያዎችን መንገድ ላይ በደፈጣ ጥቃት ጠብቀው ገድለዋል ሲል በመግለጫው መጥቀሱን ዳጉ ጆርናል ተመልክቷል።
የዞኑ መንግስት እነዚህ ህይወታቸውን ያጡ አመራርና ባለሙያ የህዝብና የመንግስትን ተልዕኮ ለማስፈፀም ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ህብረተሰቡን በልማት እና በመልካም አስተዳደር ተጠቃሚ ለማድረግ ቀን ከሌት ሲተጉ የነበሩ ቅንና ታታሪ የህዝብ ልጆች ነበሩ ብሏል።
የዞኑ መንግስት በግድያዉ ህይወታቸዉን ላጡ ቤተሰቦቻቸዉ እና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን ተመኝቷል።
#ዳጉ_ጆርናል