በዶ/ር ደብረፂዮን የሚመራዉ የህወሓት ቡድን በአንዳንድ አካባቢዎች የአስተዳደር ተቋማትን በሀይል መቆጣጠር ጀመረ‼️
ለወራት የቆየው በህወሓት አመራሮች መካከል ያለው አለመግባባት ተባብሶ እንደቀጠለ መሆኑ ተሰምቷል። ባለፉት ወራት በደብረፂዮን (ዶ/ር) የሚመራው ወገን የጊዜያዊ አስተዳደሩን ሥልጣን ለመቆጣጠር የተለያዩ እርምጃዎች ሲወስድ ቆይቷል።
በአቶ ጌታቸው የሚመራው የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደርም ይህ ሙከራ በክልሉ አለመረጋጋት በማስፈን ያለውን ችግር እንደሚያባብስ በመግለጽ ቢያስጠነቅቅም ከጊዜ ወደ ጊዜ ውጥረቱ እየተባባሰ ይገኛል ሲል ቢቢሲ አማርኛ ዘግቧል።
ባለፉት ቀናት በክልሉ ያሉት ታጣቂ ኃይሎች አመራሮች ድጋፍ እንዳለው የሚነገርለት የደብረፂዮን ቡድን በተለያዩ አካባቢዎች ያሉ የአስተዳደር ተቋማትን በኃይል የመቆጣጠር አዝማሚያ እያሳየ መሆኑ እየተገለጸ ነው።
ይህ ሁኔታም በክልሉ ዳግም ግጭት ሊያስከትል ይችላል በሚል ነዋሪዎች ላይ ከባድ ስጋትን የፈጠረ ሲሆን፣ አቅም ያላቸው ወደ አዲስ አበባ እና ወደ ሌሎች አካባቢዎች እያቀኑ መሆናቸውን ነዋሪዎች ለቢቢሲ ገልጸዋል።
በተለይ በአቶ ጌታቸው የሚመራው አስተዳደር የትግራይ ኃይልን ከሚመሩት ወታደራዊ አዛዦች መካከል ዋነኛ የሚባሉትን ሦስት መኮንኖች ማገዱን ካስታወቀ በኋላ ውጥረቱ አይሏል።
ዛሬ ማክሰኞ ረፋድ ላይ በምሥራቃዊ ዞን የጊዜያዊ አስተዳደሩን የተቃወሙ የሠራዊት አመራሮች ከመሩት እንቅስቃሴ ጋር በተያያዘ የአዲግራት ከንቲባ ጽህፈት ቤት ከጊዜያዊ አስተዳደሩ ቁጥጥር ውጪ መሆኑ ታውቋል።
ይህንን ተከትሎ በሰላማዊ ሰዎች እና በታጣቂዎች መካከል የተፈጠረ ግጭት ወይም የደረሰ ጉዳት እንዳለ አልተገለፀም።
ትናንት ሰኞ የዞኑ ሰላም እና ፀጥታ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ለአራት ሰዓታት በዶ/ር ደብረፂዮን በሚደግፉ የፀጥታ ኃይሎች ታስረው ነበር።
የአዲግራቱን ከንቲባ ጽህፈት ቤት በቁጥጥር ስር ማዋሉን ህወሓት በፌስ ቡክ ገፁ አረጋግጧል።
"የአዲግራት ከተማ ከንቲባ ሆኖ በምክር ቤት የተሾመው ረዳኢ ገብረ እግዚአብሔር በምስለኔ ግለሰቦች በተሾሙ ሰዎች ምክንያት ጽህፈት ቤቱን ተረክቦ አገልግሎት እንዳይሰጥ አደርጎ ቆይቷል" በማለት ጽህፈት ቤቱን መልሰው መቆጣጠራቸውን ገልጸዋል።
Via ቢቢሲ አማርኛ
#ዳጉ_ጆርናል
ለወራት የቆየው በህወሓት አመራሮች መካከል ያለው አለመግባባት ተባብሶ እንደቀጠለ መሆኑ ተሰምቷል። ባለፉት ወራት በደብረፂዮን (ዶ/ር) የሚመራው ወገን የጊዜያዊ አስተዳደሩን ሥልጣን ለመቆጣጠር የተለያዩ እርምጃዎች ሲወስድ ቆይቷል።
በአቶ ጌታቸው የሚመራው የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደርም ይህ ሙከራ በክልሉ አለመረጋጋት በማስፈን ያለውን ችግር እንደሚያባብስ በመግለጽ ቢያስጠነቅቅም ከጊዜ ወደ ጊዜ ውጥረቱ እየተባባሰ ይገኛል ሲል ቢቢሲ አማርኛ ዘግቧል።
ባለፉት ቀናት በክልሉ ያሉት ታጣቂ ኃይሎች አመራሮች ድጋፍ እንዳለው የሚነገርለት የደብረፂዮን ቡድን በተለያዩ አካባቢዎች ያሉ የአስተዳደር ተቋማትን በኃይል የመቆጣጠር አዝማሚያ እያሳየ መሆኑ እየተገለጸ ነው።
ይህ ሁኔታም በክልሉ ዳግም ግጭት ሊያስከትል ይችላል በሚል ነዋሪዎች ላይ ከባድ ስጋትን የፈጠረ ሲሆን፣ አቅም ያላቸው ወደ አዲስ አበባ እና ወደ ሌሎች አካባቢዎች እያቀኑ መሆናቸውን ነዋሪዎች ለቢቢሲ ገልጸዋል።
በተለይ በአቶ ጌታቸው የሚመራው አስተዳደር የትግራይ ኃይልን ከሚመሩት ወታደራዊ አዛዦች መካከል ዋነኛ የሚባሉትን ሦስት መኮንኖች ማገዱን ካስታወቀ በኋላ ውጥረቱ አይሏል።
ዛሬ ማክሰኞ ረፋድ ላይ በምሥራቃዊ ዞን የጊዜያዊ አስተዳደሩን የተቃወሙ የሠራዊት አመራሮች ከመሩት እንቅስቃሴ ጋር በተያያዘ የአዲግራት ከንቲባ ጽህፈት ቤት ከጊዜያዊ አስተዳደሩ ቁጥጥር ውጪ መሆኑ ታውቋል።
ይህንን ተከትሎ በሰላማዊ ሰዎች እና በታጣቂዎች መካከል የተፈጠረ ግጭት ወይም የደረሰ ጉዳት እንዳለ አልተገለፀም።
ትናንት ሰኞ የዞኑ ሰላም እና ፀጥታ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ለአራት ሰዓታት በዶ/ር ደብረፂዮን በሚደግፉ የፀጥታ ኃይሎች ታስረው ነበር።
የአዲግራቱን ከንቲባ ጽህፈት ቤት በቁጥጥር ስር ማዋሉን ህወሓት በፌስ ቡክ ገፁ አረጋግጧል።
"የአዲግራት ከተማ ከንቲባ ሆኖ በምክር ቤት የተሾመው ረዳኢ ገብረ እግዚአብሔር በምስለኔ ግለሰቦች በተሾሙ ሰዎች ምክንያት ጽህፈት ቤቱን ተረክቦ አገልግሎት እንዳይሰጥ አደርጎ ቆይቷል" በማለት ጽህፈት ቤቱን መልሰው መቆጣጠራቸውን ገልጸዋል።
Via ቢቢሲ አማርኛ
#ዳጉ_ጆርናል