በኢሊባቡር ዞን የአስገድዶ መድፈር ጥቃት የፈፀመዉ ግለሰብ በእስራት ተቀጣ
የኢሊባቡር ዞን ፖሊስ መምሪያ የኮሙዩኒኬሽን ፅህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ለማ ቦይዶ ለብስራት ሬዲዮ እንደተናገሩት ተከሳሽ እሸቱ ጉዲና የተባለዉ ግለሰብ ድምፅ አልባ በሆነ ስለታም ጩቤ መሳሪያ በማስፈራራት የ15 አመቷ ልጅ ላይ የአስገድዶ መድፈር ጥቃት መፈፀሙ ተገልጿል ።
ተከሳሹ ጥቃቱን የፈፀመዉ በኢሊባቡር ዞን ሱጴ ሶዶ ወረዳ ዉስጥ ታህሳስ 3 ቀን 2017 ዓ.ም ሲሆን ተጠቂዋ ለቤተሰቦቻ የደረሰባትን ጥቃት በማሳወቋ ወዲያውኑ ፖሊስ ተከሳሹን በቁጥጥር ስር ሊያዉለዉ ችሏል ። ፖሊስም ታዳጊዋን ወደ ህክምና ተቋም ወስዶ ካስመረመረ በኋላ የምርመራ መዝገቡን በተጠቂዋ ቃል በማደራጀት ለአቃቤ ህግ ልኳል ።
አቃቤ ህግም መዝገቡን በመመልከት በወንጀል ህግ ቁጥር 620 ንዑስ አንቀጽ 1 መሠረት ተጎጂዋ መከላከል በማትችልበት መንገድ በኃይልና በመሳሪያ በማስፈራራት የመድፈር ጥቃት በመፈፀም ክስ መስርቶበታል ። ክሱን ሲከታተል የቆየዉ የኢሊባቡር ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተከሳሹ የፈፀመው ድርጊት በአቃቤ ህግ ማስረጃ ጥፋተኛነቱ በመረጋገጡ የካቲት 27 ቀን 2017 ዓ.ም በዋለዉ ችሎት በ6 አመት እስራት እንዲቀጣ የተወሰነበት መሆኑን ምክትል ኢንስፔክተር ለማ ቦይዶ ጨምረዉ ለብስራት ተናግረዋል፡፡
በመባ ወርቅነህ
#ዳጉ_ጆርናል
የኢሊባቡር ዞን ፖሊስ መምሪያ የኮሙዩኒኬሽን ፅህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ለማ ቦይዶ ለብስራት ሬዲዮ እንደተናገሩት ተከሳሽ እሸቱ ጉዲና የተባለዉ ግለሰብ ድምፅ አልባ በሆነ ስለታም ጩቤ መሳሪያ በማስፈራራት የ15 አመቷ ልጅ ላይ የአስገድዶ መድፈር ጥቃት መፈፀሙ ተገልጿል ።
ተከሳሹ ጥቃቱን የፈፀመዉ በኢሊባቡር ዞን ሱጴ ሶዶ ወረዳ ዉስጥ ታህሳስ 3 ቀን 2017 ዓ.ም ሲሆን ተጠቂዋ ለቤተሰቦቻ የደረሰባትን ጥቃት በማሳወቋ ወዲያውኑ ፖሊስ ተከሳሹን በቁጥጥር ስር ሊያዉለዉ ችሏል ። ፖሊስም ታዳጊዋን ወደ ህክምና ተቋም ወስዶ ካስመረመረ በኋላ የምርመራ መዝገቡን በተጠቂዋ ቃል በማደራጀት ለአቃቤ ህግ ልኳል ።
አቃቤ ህግም መዝገቡን በመመልከት በወንጀል ህግ ቁጥር 620 ንዑስ አንቀጽ 1 መሠረት ተጎጂዋ መከላከል በማትችልበት መንገድ በኃይልና በመሳሪያ በማስፈራራት የመድፈር ጥቃት በመፈፀም ክስ መስርቶበታል ። ክሱን ሲከታተል የቆየዉ የኢሊባቡር ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተከሳሹ የፈፀመው ድርጊት በአቃቤ ህግ ማስረጃ ጥፋተኛነቱ በመረጋገጡ የካቲት 27 ቀን 2017 ዓ.ም በዋለዉ ችሎት በ6 አመት እስራት እንዲቀጣ የተወሰነበት መሆኑን ምክትል ኢንስፔክተር ለማ ቦይዶ ጨምረዉ ለብስራት ተናግረዋል፡፡
በመባ ወርቅነህ
#ዳጉ_ጆርናል