✝✞✝ እንኩዋን ለጻድቃን ቅዱሳን "አቡነ ዘርዓ ቡሩክ" : "አባ መቃርስ" እና "አባ አብራኮስ" በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✝✞✝
+*" አቡነ ዘርዓ ቡሩክ "*+
=>ሃገራችን ኢትዮዽያ:-
*ብሉይ ከሐዲስ ያልጐደለባት
*በክርስቶስና በድንግል እናቱ ኪደተ እግር የተቀደሰች
*የቅዱሳን መጠጊያ እና
*ብዙ ቅዱሳንን ከእቅፏ ያፈራች ስለ ሆነች የተባረከች ሃገር ትባላለች::
+ሁሉም የሃገራችን ክፍሎች ቅዱሳንን አፍርተዋል:: በምሥራቅም: በምዕራብም: በሰሜንም: በደቡብም ያሉ አካባቢዎች ሁሉ የቅዱሳን ቤቶች ናቸው:: ቅዱሳንን በብዛት ካፈሩ አካባቢዎች አንዱ ደግሞ ምድረ ጐጃም ነው::
+በጐጃም አካባቢ ከተነሱ ቅዱሳን ደግሞ አንዱና ስመ ጥሩ ጻድቅ አቡነ ዘርዓ ቡሩክ ናቸው:: አቡነ ዘርዓ ቡሩክ በብዙ ጐዳና የተለዩ አባት ናቸው:: ለመጥቀስ ያህል እንኩዋ:-
1.በታሪክ ዓለምን ከበው የያዙ 2ቱ ግሩማን አራዊት (ብሔሞትና ሌዋታንን) ጥርስ ቆጥረው: ብዙ ምሥጢራትንም ተመልክተው ተመልሰዋል:: (በነገራችሁ ላይ ይህ ጉዳይ ዛሬም ድረስ ሳይንሱ በብዙ ድካም ያልደረሰበት ነው)
2.ጻድቁ በልደታቸው ጊዜ ዓይነ ስውራንን አብርተዋል:: ለራሳቸው ግን ይህን የግፍ ዓለም ላለማየት ጸልየው ዓይናቸው እንዲጠፋ አድርገዋል::
3.መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚል ቅዱስ ኢያሱ በገባኦን ፀሐይን አቁሟል:: ዘርዓ ቡሩክ ግን በጥበበ እግዚአብሔር ፀሐይን ለ5 ዓመት አቁመዋል::
4.ጻድቁ ከንጽሕናቸው ብዛት 12 ክንፍ (መንፈሳዊ ክንፍ) ተሰጥቷቸው ነበር:: ከዚህ በተረፈም በጾም: በጸሎት: በትርምትና በስብከተ ወንጌል ፍጹም ጽሙድ ነበሩ::
+ጻድቁ የተወለዱት በ16ኛው መቶ ክ/ዘ እዚያው ጐጃም ውስጥ ሲሆን አባታቸው ደመ ክርስቶስ: እናታቸው ደግሞ ማርያም ሞገሳ ይባላሉ:: ወላጆች በልጅ እጦት ተማለው ይህን የተቀደሰ ፍሬ አገኙ:: "ጸጋ ኢየሱስ" ብለውታል:: ከኢየሱስ ክርስቶስ ተሰጥቷቸዋልና::
+ቀጥሎ የወለዱትንም "ተስፋ ኢየሱስ" ብለውታል:: ይህም የጻድቁ ታናሽ ወንድም ነው:: በሒደት ግን የጸጋ ኢየሱስ ስም በፈቃደ እግዚአብሔር ወደ ዘርዓ ቡሩክነት ተቀይሯል:: ጻድቁን ስመ ጥር ካደረጉዋቸው ሥራዎቻቸው መካከል በአፄ ሱስንዮስ ዘመን የሠሩት ቅድሚያውን ይወስዳል::
+ነገሩ እንዲህ ነው:: በ1598 ዓ/ም በኢትዮዽያ ላይ የነገሡት አፄ ሱስንዮስ ዼጥሮስ (ፔድሮ) ፓኤዝ ከሚባል ፈረንጅ መናፍቅ ጋር በፈጠሩት ወዳጅነት ሃይማኖታቸውን ለወጡ:: ካቶሊክ (ሮማዊ)ም ሆኑ::
+በሁዋላም አልፎንሱ ሜንዴዝ የሚሉት እሾህ መጥቶ ሁሉም የኢትዮዽያ ሕዝብ መናፍቅ እንዲሆን ከንጉሡ ጋር መከረ:: ለጊዜው በቤተ መንግስቱ አካባቢ የነበሩ መሣፍንት ተቀላቀሉ:: እየቆየ ግን ዜናው በመላ ሃገሪቱ ተሰማ::
+በተለይ በ1611 በተዋሕዶ አማኞችና በመናፍቁ ንጉሥ መካከል ነገሩ ተካሮ ዻዻሱ አቡነ ስምዖን ጠዳ ላይ መገደላቸው ተሰማ:: በዚህ ጊዜ ገበሬው ከእርሻው: ሴቷ ከማዕድ ቤት: ካህኑ ከመቅደሱ: ነጋዴው ከገበያው እየወጡ ስለ ቀናችው ሃይማኖት ደማቸውን አፈሰሱ::
+በበዓት የተወሰኑ በሺህ የሚቆጠሩ ቅዱሳንም ወጥተው ተሰየፉ:: በዚህ ጊዜም የግሺው አቡነ ዘርዓ ቡሩክ ዳዊታቸውን አንግበው ለሰማዕትነት ሔዱ:: ዓባይ ወንዝ ላይ ሲደርሱ ዳዊታቸውን ወደ ወንዙ ውስጥ ጣሉት::
+ተሻግረውም ከንጉሡ አደባባይ ደንቀዝ ደረሱ:: በጊዜውም ልክ እንደነ ፍቅርተ ክርስቶስና ወለተ ዼጥሮስ እርሳቸውም መከራ ደረሰባቸው:: ንጉሡም ሳይገደሉ እንዲታሠሩ አደረገ:: በጨለማ እስር ቤትም 5 ዓመታትን ሲያሳልፉ ትኩስ ምግብን ያመጡላቸው ነበር::
+እርሳቸው ግን ምግባቸው ሰማያዊ ነበርና አልነኩትም:: ከ5 ዓመት በሁዋላም ያ ሁሉ ምግብ በተአምራት በትኩስነቱ እየጨሰ ተገኝቷል:: ዘርዓ ቡሩክም ከእሥር ተፈትተዋል::
+እግዚአብሔርም በከሐዲው ንጉሥ ላይ ፈርዶ ፋሲል ነግሷል:: ሃይማኖት ተመልሷል:: ጻድቁም በዓባይ ወንዝ ላይ የጣሉት ዳዊታቸውን ሳይርስ አግኝተውታል::
+ጐጃም ሲደርሱም ሰይጣን እርሳቸውን መስሎ ሲያስት ስላገኙት ወደ ጥልቁ አስጥመውታል:: በተረፈ ዘመናቸው አቡነ ዘርዓ ቡሩክ ብዙ ተጋድለው ጥር 13 ቀን ዐርፈዋል::
>
+"+ አባ መቃርስ ገዳማዊ +"+
=>"መቃርስ" የሚለው ቃል በዮናኒ ልሳን "ብጹዕ" እንደ ማለት ሲሆን የመነኮሳት አለቃ ቅዱስ መቃርስን ጨምሮ በርካታ ቅዱሳን በስሙ ተጠርተውበታል:: በነገረ ቅዱሳን ታዋቂ ከሆኑት አንዱና ተጠቃሹ ዛሬ የምናከብረው አባት ሲሆን ብዙ ጊዜ "ዘይሴሰይ ቆቅሃ - ቆቅን የሚበላው" እየተባለ ይጠራል::
+የዚህንም ምክንያቱን እንመለከታለን:: ቅዱስ መቃርስ በ5ኛው መቶ ክ/ዘመን በምድረ ግብጽ የነበረ የዘመነ ጻድቃን ፍሬ ነው:: ከእሱ በፊት ታላቁ መቃርስ: መቃርስ ቀሲስና መቃርስ ዘቃው የተባሉ አባቶች ስለ ነበሩ እርሱን 4ኛው መቃርስ እያሉ መጥራት የተለመደ ነው::
+በወጣትነቱ ከዓለም ወጥቶ ገዳም ገባ:: ቀጥሎም መነኮሰ:: ግን ግን ወሬን: ሐሜትንና ትዕቢትን ፈጽሞ ይጠላ ነበርና: ከገዳሙ ወጥቶ ሰው ወደማይኖርበት በርሃ ሔደ::
+ግን በአካባቢው የሚበላ ነገር: ከዛፍ ፍሬ: ከሣር ዘርም እንኩዋ ምንም ነገርን ማግኘት አልቻለም:: ጾሞ በራበው ጊዜም "ፍጥረትን የምትመግብ ጌታ ሆይ! ራቴን አብላኝ?" ሲል ጸለየ::
+እግዚአብሔርም አንዲት ቆቅን አምጥቶለት በላ:: ከዚህ በሁዋላም ምግቡ ቆቅ ብቻ ሆነ:: ማታ ማታ 1 ቆቅ ይያዝለታል:: እርሱም አመስግኖ እየበላ ዘመናት አለፉ::
+እግዚአብሔር የዚህ ገዳማዊ ዜና እንዲገለጥ ስለ ፈለገ አንድ የቁስጥንጥንያ መነኮስ ከሃገሩ ተነስቶ ወደ በርሃ ወረደ:: መጠለያ በዓት ሲፈልግም አንድ አረጋዊ ባሕታዊ ቆቅ ሲያጠምድ ተመልክቶ ደነገጠ::
+"መነኮስ ሆኖ እንዴት ሥጋ ይበላል" ሲልም ተናደደ:: ነገሩን ለሊቀ ዻዻሳቱ ይነግር ዘንድም በመጣበት መንገድ እየቸኮለ ተመለሰ:: የሃገሩን ፓትርያርክም "አባታችን አንድ ባሕታዊ እምነታችን ሊያሰድብ እንዲህ አደረገኮ" ቢለው ነገሩ እርግጥ ይሆን ዘንድ ፓትርያርኩ አንድ ሰው ጨምሮ 2ቱን ላካቸው::
+በዚያች ቀንም ቅዱስ መቃርስ ለመጀመሪያ ጊዜ 3 ቆቆች ገቡለት:: "ጌታየ! 2ቱን ምን ላድርጋቸው?" ሲል መነኮሳቱ ወደ እርሱ ደረሱ:: ደስ ብሎት ፈጣሪን እያመሰገነ ሠርቶ አቀረበላቸው::
+እነርሱ ግን ቅዱሱን ናቁት:: "አንበላም" አሉት:: አባ መቃርስም የተጠበሱት ቆቆች እፍ እፍ እያለ ነፍስ ዘራባቸውና እንዲበሩ አደረገ:: በዚህ የደነገጡት መነኮሳቱ ሰግደውለት እየተሯሯጡ ወደ ሃገራቸው ተመለሱ::
+ባሙበት አፋቸው "ታላቅ ሰው ተገኝቷል: በረከቱ አይለፋችሁ" ሲሉ ሰበኩ:: ይህ ሲሰማም ፓትርያርኩ ከነ ሕዝቡ: ንጉሡ ከነ ሠራዊቱ ሊባረኩ ወደ በርሃው ወረዱ:: ግን ቅዱስ መልአክ ተሸክሞት ወደ ብሔረ ሕያዋን ሲያርግ ደረሱ::
+እየጮሁ "አባ በረከትህን: የድህነት ቃልህን?" አሉት:: እርሱም "ይጹም አፉክሙ እምነገረ ውዴት ወሐሜት - አፋችሁ ከሐሜት: ከነገር ሥራት ይጹም:: ካህናት ትምሕርት: መነኮሳት ትሕርምትን አታብዙ:: ልቡናችሁ አይታበይ:: ሰላም ለእናንተ ይሁን!" ብሏቸው ከዐይናቸው ተሰወረ:: ወደ ብሔረ ሕያዋንም ገባ::
+"+ አባ አብራኮስ ገዳማዊ +"+
+*" አቡነ ዘርዓ ቡሩክ "*+
=>ሃገራችን ኢትዮዽያ:-
*ብሉይ ከሐዲስ ያልጐደለባት
*በክርስቶስና በድንግል እናቱ ኪደተ እግር የተቀደሰች
*የቅዱሳን መጠጊያ እና
*ብዙ ቅዱሳንን ከእቅፏ ያፈራች ስለ ሆነች የተባረከች ሃገር ትባላለች::
+ሁሉም የሃገራችን ክፍሎች ቅዱሳንን አፍርተዋል:: በምሥራቅም: በምዕራብም: በሰሜንም: በደቡብም ያሉ አካባቢዎች ሁሉ የቅዱሳን ቤቶች ናቸው:: ቅዱሳንን በብዛት ካፈሩ አካባቢዎች አንዱ ደግሞ ምድረ ጐጃም ነው::
+በጐጃም አካባቢ ከተነሱ ቅዱሳን ደግሞ አንዱና ስመ ጥሩ ጻድቅ አቡነ ዘርዓ ቡሩክ ናቸው:: አቡነ ዘርዓ ቡሩክ በብዙ ጐዳና የተለዩ አባት ናቸው:: ለመጥቀስ ያህል እንኩዋ:-
1.በታሪክ ዓለምን ከበው የያዙ 2ቱ ግሩማን አራዊት (ብሔሞትና ሌዋታንን) ጥርስ ቆጥረው: ብዙ ምሥጢራትንም ተመልክተው ተመልሰዋል:: (በነገራችሁ ላይ ይህ ጉዳይ ዛሬም ድረስ ሳይንሱ በብዙ ድካም ያልደረሰበት ነው)
2.ጻድቁ በልደታቸው ጊዜ ዓይነ ስውራንን አብርተዋል:: ለራሳቸው ግን ይህን የግፍ ዓለም ላለማየት ጸልየው ዓይናቸው እንዲጠፋ አድርገዋል::
3.መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚል ቅዱስ ኢያሱ በገባኦን ፀሐይን አቁሟል:: ዘርዓ ቡሩክ ግን በጥበበ እግዚአብሔር ፀሐይን ለ5 ዓመት አቁመዋል::
4.ጻድቁ ከንጽሕናቸው ብዛት 12 ክንፍ (መንፈሳዊ ክንፍ) ተሰጥቷቸው ነበር:: ከዚህ በተረፈም በጾም: በጸሎት: በትርምትና በስብከተ ወንጌል ፍጹም ጽሙድ ነበሩ::
+ጻድቁ የተወለዱት በ16ኛው መቶ ክ/ዘ እዚያው ጐጃም ውስጥ ሲሆን አባታቸው ደመ ክርስቶስ: እናታቸው ደግሞ ማርያም ሞገሳ ይባላሉ:: ወላጆች በልጅ እጦት ተማለው ይህን የተቀደሰ ፍሬ አገኙ:: "ጸጋ ኢየሱስ" ብለውታል:: ከኢየሱስ ክርስቶስ ተሰጥቷቸዋልና::
+ቀጥሎ የወለዱትንም "ተስፋ ኢየሱስ" ብለውታል:: ይህም የጻድቁ ታናሽ ወንድም ነው:: በሒደት ግን የጸጋ ኢየሱስ ስም በፈቃደ እግዚአብሔር ወደ ዘርዓ ቡሩክነት ተቀይሯል:: ጻድቁን ስመ ጥር ካደረጉዋቸው ሥራዎቻቸው መካከል በአፄ ሱስንዮስ ዘመን የሠሩት ቅድሚያውን ይወስዳል::
+ነገሩ እንዲህ ነው:: በ1598 ዓ/ም በኢትዮዽያ ላይ የነገሡት አፄ ሱስንዮስ ዼጥሮስ (ፔድሮ) ፓኤዝ ከሚባል ፈረንጅ መናፍቅ ጋር በፈጠሩት ወዳጅነት ሃይማኖታቸውን ለወጡ:: ካቶሊክ (ሮማዊ)ም ሆኑ::
+በሁዋላም አልፎንሱ ሜንዴዝ የሚሉት እሾህ መጥቶ ሁሉም የኢትዮዽያ ሕዝብ መናፍቅ እንዲሆን ከንጉሡ ጋር መከረ:: ለጊዜው በቤተ መንግስቱ አካባቢ የነበሩ መሣፍንት ተቀላቀሉ:: እየቆየ ግን ዜናው በመላ ሃገሪቱ ተሰማ::
+በተለይ በ1611 በተዋሕዶ አማኞችና በመናፍቁ ንጉሥ መካከል ነገሩ ተካሮ ዻዻሱ አቡነ ስምዖን ጠዳ ላይ መገደላቸው ተሰማ:: በዚህ ጊዜ ገበሬው ከእርሻው: ሴቷ ከማዕድ ቤት: ካህኑ ከመቅደሱ: ነጋዴው ከገበያው እየወጡ ስለ ቀናችው ሃይማኖት ደማቸውን አፈሰሱ::
+በበዓት የተወሰኑ በሺህ የሚቆጠሩ ቅዱሳንም ወጥተው ተሰየፉ:: በዚህ ጊዜም የግሺው አቡነ ዘርዓ ቡሩክ ዳዊታቸውን አንግበው ለሰማዕትነት ሔዱ:: ዓባይ ወንዝ ላይ ሲደርሱ ዳዊታቸውን ወደ ወንዙ ውስጥ ጣሉት::
+ተሻግረውም ከንጉሡ አደባባይ ደንቀዝ ደረሱ:: በጊዜውም ልክ እንደነ ፍቅርተ ክርስቶስና ወለተ ዼጥሮስ እርሳቸውም መከራ ደረሰባቸው:: ንጉሡም ሳይገደሉ እንዲታሠሩ አደረገ:: በጨለማ እስር ቤትም 5 ዓመታትን ሲያሳልፉ ትኩስ ምግብን ያመጡላቸው ነበር::
+እርሳቸው ግን ምግባቸው ሰማያዊ ነበርና አልነኩትም:: ከ5 ዓመት በሁዋላም ያ ሁሉ ምግብ በተአምራት በትኩስነቱ እየጨሰ ተገኝቷል:: ዘርዓ ቡሩክም ከእሥር ተፈትተዋል::
+እግዚአብሔርም በከሐዲው ንጉሥ ላይ ፈርዶ ፋሲል ነግሷል:: ሃይማኖት ተመልሷል:: ጻድቁም በዓባይ ወንዝ ላይ የጣሉት ዳዊታቸውን ሳይርስ አግኝተውታል::
+ጐጃም ሲደርሱም ሰይጣን እርሳቸውን መስሎ ሲያስት ስላገኙት ወደ ጥልቁ አስጥመውታል:: በተረፈ ዘመናቸው አቡነ ዘርዓ ቡሩክ ብዙ ተጋድለው ጥር 13 ቀን ዐርፈዋል::
>
+"+ አባ መቃርስ ገዳማዊ +"+
=>"መቃርስ" የሚለው ቃል በዮናኒ ልሳን "ብጹዕ" እንደ ማለት ሲሆን የመነኮሳት አለቃ ቅዱስ መቃርስን ጨምሮ በርካታ ቅዱሳን በስሙ ተጠርተውበታል:: በነገረ ቅዱሳን ታዋቂ ከሆኑት አንዱና ተጠቃሹ ዛሬ የምናከብረው አባት ሲሆን ብዙ ጊዜ "ዘይሴሰይ ቆቅሃ - ቆቅን የሚበላው" እየተባለ ይጠራል::
+የዚህንም ምክንያቱን እንመለከታለን:: ቅዱስ መቃርስ በ5ኛው መቶ ክ/ዘመን በምድረ ግብጽ የነበረ የዘመነ ጻድቃን ፍሬ ነው:: ከእሱ በፊት ታላቁ መቃርስ: መቃርስ ቀሲስና መቃርስ ዘቃው የተባሉ አባቶች ስለ ነበሩ እርሱን 4ኛው መቃርስ እያሉ መጥራት የተለመደ ነው::
+በወጣትነቱ ከዓለም ወጥቶ ገዳም ገባ:: ቀጥሎም መነኮሰ:: ግን ግን ወሬን: ሐሜትንና ትዕቢትን ፈጽሞ ይጠላ ነበርና: ከገዳሙ ወጥቶ ሰው ወደማይኖርበት በርሃ ሔደ::
+ግን በአካባቢው የሚበላ ነገር: ከዛፍ ፍሬ: ከሣር ዘርም እንኩዋ ምንም ነገርን ማግኘት አልቻለም:: ጾሞ በራበው ጊዜም "ፍጥረትን የምትመግብ ጌታ ሆይ! ራቴን አብላኝ?" ሲል ጸለየ::
+እግዚአብሔርም አንዲት ቆቅን አምጥቶለት በላ:: ከዚህ በሁዋላም ምግቡ ቆቅ ብቻ ሆነ:: ማታ ማታ 1 ቆቅ ይያዝለታል:: እርሱም አመስግኖ እየበላ ዘመናት አለፉ::
+እግዚአብሔር የዚህ ገዳማዊ ዜና እንዲገለጥ ስለ ፈለገ አንድ የቁስጥንጥንያ መነኮስ ከሃገሩ ተነስቶ ወደ በርሃ ወረደ:: መጠለያ በዓት ሲፈልግም አንድ አረጋዊ ባሕታዊ ቆቅ ሲያጠምድ ተመልክቶ ደነገጠ::
+"መነኮስ ሆኖ እንዴት ሥጋ ይበላል" ሲልም ተናደደ:: ነገሩን ለሊቀ ዻዻሳቱ ይነግር ዘንድም በመጣበት መንገድ እየቸኮለ ተመለሰ:: የሃገሩን ፓትርያርክም "አባታችን አንድ ባሕታዊ እምነታችን ሊያሰድብ እንዲህ አደረገኮ" ቢለው ነገሩ እርግጥ ይሆን ዘንድ ፓትርያርኩ አንድ ሰው ጨምሮ 2ቱን ላካቸው::
+በዚያች ቀንም ቅዱስ መቃርስ ለመጀመሪያ ጊዜ 3 ቆቆች ገቡለት:: "ጌታየ! 2ቱን ምን ላድርጋቸው?" ሲል መነኮሳቱ ወደ እርሱ ደረሱ:: ደስ ብሎት ፈጣሪን እያመሰገነ ሠርቶ አቀረበላቸው::
+እነርሱ ግን ቅዱሱን ናቁት:: "አንበላም" አሉት:: አባ መቃርስም የተጠበሱት ቆቆች እፍ እፍ እያለ ነፍስ ዘራባቸውና እንዲበሩ አደረገ:: በዚህ የደነገጡት መነኮሳቱ ሰግደውለት እየተሯሯጡ ወደ ሃገራቸው ተመለሱ::
+ባሙበት አፋቸው "ታላቅ ሰው ተገኝቷል: በረከቱ አይለፋችሁ" ሲሉ ሰበኩ:: ይህ ሲሰማም ፓትርያርኩ ከነ ሕዝቡ: ንጉሡ ከነ ሠራዊቱ ሊባረኩ ወደ በርሃው ወረዱ:: ግን ቅዱስ መልአክ ተሸክሞት ወደ ብሔረ ሕያዋን ሲያርግ ደረሱ::
+እየጮሁ "አባ በረከትህን: የድህነት ቃልህን?" አሉት:: እርሱም "ይጹም አፉክሙ እምነገረ ውዴት ወሐሜት - አፋችሁ ከሐሜት: ከነገር ሥራት ይጹም:: ካህናት ትምሕርት: መነኮሳት ትሕርምትን አታብዙ:: ልቡናችሁ አይታበይ:: ሰላም ለእናንተ ይሁን!" ብሏቸው ከዐይናቸው ተሰወረ:: ወደ ብሔረ ሕያዋንም ገባ::
+"+ አባ አብራኮስ ገዳማዊ +"+