ሁለት ገፅታ (ክፍል ሦስት)
(በኹሉድ ኑሪ)
....ሁለታችንም ሮጠን ወደዚያው ሄድን። ስንቀርብ የወደቀችው ሴት መሆኗን አወቅን ስለጨለመ ግን ማንነቷን መለየት ባንችልም እኔ ግን ፍርዲ ትሆናለች ብዬ ነበር የገመትኩት እጇ በደም ተለውሷል አንስተናት ወደ Hospital ሄድን የገመትኩት ልክ ነበር ልጅቷ ፍርዶውስ ናት ፊቷ በላልዟል ዶከተሮች ተቀብለውን ወደውስጥ አስገቧት እኔ እና ዓሊም ገንዘብ ለመክፈልና ካርድ ለማውጣት ሄድን ካርድ መዝጋቢዋ "የpatientዋን ስም"ስትለኝ "ፍርዶውስ" አልኳት እና ማልቀስ ጀመርኩ ዓሊም እሷ እንደሆነች ሲያውቅ በጣም ደነገጠ እንድረጋጋ ተቆጥቶ ተናገረኝ።የካርዱን ጣጣ እንደጨረስን ወደ ፍርዲ ስንሄድ ዶክተሩ ቢሮው አስጠራንና "ፍርዶውስ እራሷን ለማጥፋት ምን እንዳነሳሳት ጠየቀን" ሆኖም መልሳችን "አናውቅም"ነበር እሱም ፍርደውስ የእጅ ደምስሯን ቆርጣው ቢሆንም በጊዜ ይዘናት ስለመጣን ሕይወቷን መታደግ እንደቻልንና የዚህ አይነት ነገር ዳግመኛ እንዳይፈጠር ወደpsychiatry ይዘናት መሄድ እንዳለብን እና ሲነጋ ይዘናት መሄድ እንደምንችል ነገረን።እኔ እና ዓሊ እዛው አድረን ሲነጋ ፍርዲን ወደ እኛ ቤት ይዘናት ሄድን ይኼ ሁሉ ሲሆን እሷ አንድም ቃል ከአፏ አልወጣም ስንወስዳት መሄድ፣ስናስቀምጣት መቀመጥ ነበር ስራዋ።እኔ እና ዓሊ ግራ እንደተጋባን ፍርዲም ሳታናግረን መሽቶ ነጋ ዓሊ ጥሎኝ መሄድ ባይፈልግም መሄዱ ግድ ስለሆነበት ወደስራው ሄደ እኔ ግን ይሄን አጋጣሚ ፍርዲን ለማነጋገር ምቹ ስለሆነልኝ ወዳለችበት ክፍል አቀናው ወደ ክፍሏ በተጠጋው ቁጥር ስቅ ስቅ የሚል ድምፅ ይሰማኛል በጣም ደንግጬ ሮጬ በሩን ስከፍተው ደንግጣ ጋደም ካለችበት አልጋ ብድግ አለች እና እንባዋን በሁለት እጇ ጠረገችው። "ውይ አፉ በይኝ እኔ ኮ ድምፅ ስሰማ ምን ሆና ነው ብዬ ሁፍፍ አልሃምዱሊላህ ደህና ነሽ አደል?" አልኳት ፈገግ ብላ ጭንቅላቷን በአወንታ ነቀነቀችልኝ በጣም ደስ እያለኝ"እሺ ምትፈልጊው ነገር አለ?" አልኳት ወድያውኑ ብድግ አለችና በእጄ የያዝኩትን ብር ጠቁማ እጇን ዘረጋችልኝ "ምን ብር ነው ለምንሽ ማለቴ የኔ ቆንጆ ተጎድተሻል እኮ መውጣት አችይም ቢያንስ ትንሽ ጉልበት ማግኘት አለብሽ" አልኳት ጭንቅላቷን ነቀነቀችው ቅር እያለኝ 50 ብር ስሰጣት ከእጄ ምንትፍ አድርጋ ጃኬቷን ደርባ ወጣች እኔ ቢያንስ ከኋላዋ መከተል እንዳለብኝ ተሰምቶኝ በሩን ቀስ ብዬ ዘጋግቼ ከኋላዋ ተከትያት ወጣውና ግራናቀኝ ሳይ ፍርዲ ዛፋ ጋር ቁጭ ብላ እያጨሰች ነው።ቀስ እያልኩኝ ወዳለችበት ተጠግቼ አጠገቧ ቁጭ አልኩኝ የዚህን ጊዜ ነበር ፍርዲ የመጀመሪያ ቃሏን ከአፏ ያወጣችው..የጠየቀችኝን ጥያቄዎች መልስ መስጠት አቃተኝ እውነትም ግን ሕይወት ምንድናት?፣እውነተኛ ደስታ ምንድን ነው?፣ እኔ ማን ነኝ?፣..እኔስ ምንድን ነኝ?፣..ለምን እዚህች ምድር ላይ መጣው?እነዚህን ጥያቄዎች ለራሴ እንድጠይቅ አደረገችኝ ጥያቄው ሲያዩት ቀላል ሲመልሱት ግን ከባድ ነው። ፍርዲ እጇ ላይ ያለውን ሲጋራ ሳብ ሳብ አደረገችና መናገሯን ቀጠለች "ይኼውልሽ አንድ ጥግ ላይ ብቻዬን ተቀምጫለው በልቤ ጮኼ እያለቀሰኩ ነው በዙሪያዬ ሁሉም ሰዎች አሉ ግን ጩኸቴን ለቅሶዬን ማንም የሰማው የለም አንዳንዶቹ በሽተኛ ነች ይሉኛል አንዳንዶቹ ዲዳ ናት ይሉኛል አንዳንዶቹ ዱርዬ ሰካራም ናት ይሉኛል
ግን ማንም በጭራሽ አይረዳኝም የሆነ አለ አደል መናገር ማስረዳት የማልችለው ስሜት አለ በሰውነቴ በእጄ ላይ ለሚፈጠሩት ጠባሳዎች ሀፍረት ይሰማኛል ነገር ግን በሌላ ቀን መልሼ አደርገዋለሁ ታውቂያለሽ እኔ ላስረዳው በማልችለው ነገር ተጎጂ ነኝ ግን እኔነቴን ማንም አያየውም የሆነ የተሰወረ ነገር አለ መሰለኝ እናም በቃ ህመሜን ማንም አያስተውልም እያንዳንዱ ሰው እኮ የማይናገረው የራሱ የሆኑ ችግሮችን ያልፋል እርስ በእርስ ደግ መሆን ቅን መሆን ያን ያህል ከባድ ነው እንዴ? በፊት ልጆች እያለን የሚያስጨንቀን እና የሚያሳዝነን ስሜቶችን ለማጠብ እንባዎቻችን ምቹ ነበሩ ፡፡ ስናድግ ግን የሆነ በጭራሽ በእንባ ሊታጠቡ የማይችሉ በጭራሽ መታጠብ ማይገባቸው የሚያሰቃዩ ትዝታዎች ፣በጣም የሚያሳዝዝኑ፣ የሚጎዱ፣ የሚሰብሩ፣ነገሮች እንዳሉ እንማራለን፡፡ ስለዚህ አንዳንዳንዶቻችን ማልቀስ ስንፈልግ እንስቃለን፣ማውራት እየፈለግን ዝም እንላለን፡፡ ዝም ብለን እየሳቅን ሁሉንም ህመምና ሀዘን እንቋቋማለን ሲበዛና ከአቅማችን በላይ ሲሆን ደሞ ራሳችንን ሱስ ውስጥ እንደብቃለን፡፡" ብላ ማልቀስ ጀመረች። ፍርዲ ልክ ናት ፍርዲ አዋቂ ናት ምትናገረው ነገር በሙሉ ልክ ነው ወላሂ በራሴ አዘንኩ፣ሰው መባሌ አስጠላኝ፣ አንገቴን አስደፋችኝ ከረጅም ዝምታ በኋላ የያዘችውን ያለቀ ሲጋራ ጥላ እጇን ጠራረገችና "ፍርዶውስ" አለችኝ ፈገግ ብዬ "ሰብሪን"አልኳት "ይቅርታ እንግዲህ ብሶቴን ተወጣውብሽ አንዳንዴ አዳማጭ ጆሮ ስታገኚ ገባሽ ደስ ይላል ብቻ አመሰግናለሁ ስላወቅኩሽ ደስ ብሎኛል"ብላ ፈገግ አለች"ፍርዲ እኔ አንቺን ከዚህ በላይ ማወቅ እፈልጋለው ስለራስሽ ብትነግሪኝ ደስ ይለኛል" ስላት "አየችኝ እና እርግጠኛ ነሽ ስለኔ መስማት ትፈልጊያለሽ" አለችኝ ውስጧ ላይ የተሰማት ደስታ ፊቷ ላይ ወጣ በጣም ብዙ ነገር መናገር እንደምትፈልግና እውነትም ጭንቀቷን ብሶቷን ሰምቶ ሸክሟን የሚያቀልላት ሰው እንደምትፈልግ ተረዳሁ "በደስታ ነዋ ለዛውም የምሰማሽ" ብዬ ፈገግ አልኩኝ.....ይቀጥላል
(በኹሉድ ኑሪ)
....ሁለታችንም ሮጠን ወደዚያው ሄድን። ስንቀርብ የወደቀችው ሴት መሆኗን አወቅን ስለጨለመ ግን ማንነቷን መለየት ባንችልም እኔ ግን ፍርዲ ትሆናለች ብዬ ነበር የገመትኩት እጇ በደም ተለውሷል አንስተናት ወደ Hospital ሄድን የገመትኩት ልክ ነበር ልጅቷ ፍርዶውስ ናት ፊቷ በላልዟል ዶከተሮች ተቀብለውን ወደውስጥ አስገቧት እኔ እና ዓሊም ገንዘብ ለመክፈልና ካርድ ለማውጣት ሄድን ካርድ መዝጋቢዋ "የpatientዋን ስም"ስትለኝ "ፍርዶውስ" አልኳት እና ማልቀስ ጀመርኩ ዓሊም እሷ እንደሆነች ሲያውቅ በጣም ደነገጠ እንድረጋጋ ተቆጥቶ ተናገረኝ።የካርዱን ጣጣ እንደጨረስን ወደ ፍርዲ ስንሄድ ዶክተሩ ቢሮው አስጠራንና "ፍርዶውስ እራሷን ለማጥፋት ምን እንዳነሳሳት ጠየቀን" ሆኖም መልሳችን "አናውቅም"ነበር እሱም ፍርደውስ የእጅ ደምስሯን ቆርጣው ቢሆንም በጊዜ ይዘናት ስለመጣን ሕይወቷን መታደግ እንደቻልንና የዚህ አይነት ነገር ዳግመኛ እንዳይፈጠር ወደpsychiatry ይዘናት መሄድ እንዳለብን እና ሲነጋ ይዘናት መሄድ እንደምንችል ነገረን።እኔ እና ዓሊ እዛው አድረን ሲነጋ ፍርዲን ወደ እኛ ቤት ይዘናት ሄድን ይኼ ሁሉ ሲሆን እሷ አንድም ቃል ከአፏ አልወጣም ስንወስዳት መሄድ፣ስናስቀምጣት መቀመጥ ነበር ስራዋ።እኔ እና ዓሊ ግራ እንደተጋባን ፍርዲም ሳታናግረን መሽቶ ነጋ ዓሊ ጥሎኝ መሄድ ባይፈልግም መሄዱ ግድ ስለሆነበት ወደስራው ሄደ እኔ ግን ይሄን አጋጣሚ ፍርዲን ለማነጋገር ምቹ ስለሆነልኝ ወዳለችበት ክፍል አቀናው ወደ ክፍሏ በተጠጋው ቁጥር ስቅ ስቅ የሚል ድምፅ ይሰማኛል በጣም ደንግጬ ሮጬ በሩን ስከፍተው ደንግጣ ጋደም ካለችበት አልጋ ብድግ አለች እና እንባዋን በሁለት እጇ ጠረገችው። "ውይ አፉ በይኝ እኔ ኮ ድምፅ ስሰማ ምን ሆና ነው ብዬ ሁፍፍ አልሃምዱሊላህ ደህና ነሽ አደል?" አልኳት ፈገግ ብላ ጭንቅላቷን በአወንታ ነቀነቀችልኝ በጣም ደስ እያለኝ"እሺ ምትፈልጊው ነገር አለ?" አልኳት ወድያውኑ ብድግ አለችና በእጄ የያዝኩትን ብር ጠቁማ እጇን ዘረጋችልኝ "ምን ብር ነው ለምንሽ ማለቴ የኔ ቆንጆ ተጎድተሻል እኮ መውጣት አችይም ቢያንስ ትንሽ ጉልበት ማግኘት አለብሽ" አልኳት ጭንቅላቷን ነቀነቀችው ቅር እያለኝ 50 ብር ስሰጣት ከእጄ ምንትፍ አድርጋ ጃኬቷን ደርባ ወጣች እኔ ቢያንስ ከኋላዋ መከተል እንዳለብኝ ተሰምቶኝ በሩን ቀስ ብዬ ዘጋግቼ ከኋላዋ ተከትያት ወጣውና ግራናቀኝ ሳይ ፍርዲ ዛፋ ጋር ቁጭ ብላ እያጨሰች ነው።ቀስ እያልኩኝ ወዳለችበት ተጠግቼ አጠገቧ ቁጭ አልኩኝ የዚህን ጊዜ ነበር ፍርዲ የመጀመሪያ ቃሏን ከአፏ ያወጣችው..የጠየቀችኝን ጥያቄዎች መልስ መስጠት አቃተኝ እውነትም ግን ሕይወት ምንድናት?፣እውነተኛ ደስታ ምንድን ነው?፣ እኔ ማን ነኝ?፣..እኔስ ምንድን ነኝ?፣..ለምን እዚህች ምድር ላይ መጣው?እነዚህን ጥያቄዎች ለራሴ እንድጠይቅ አደረገችኝ ጥያቄው ሲያዩት ቀላል ሲመልሱት ግን ከባድ ነው። ፍርዲ እጇ ላይ ያለውን ሲጋራ ሳብ ሳብ አደረገችና መናገሯን ቀጠለች "ይኼውልሽ አንድ ጥግ ላይ ብቻዬን ተቀምጫለው በልቤ ጮኼ እያለቀሰኩ ነው በዙሪያዬ ሁሉም ሰዎች አሉ ግን ጩኸቴን ለቅሶዬን ማንም የሰማው የለም አንዳንዶቹ በሽተኛ ነች ይሉኛል አንዳንዶቹ ዲዳ ናት ይሉኛል አንዳንዶቹ ዱርዬ ሰካራም ናት ይሉኛል
ግን ማንም በጭራሽ አይረዳኝም የሆነ አለ አደል መናገር ማስረዳት የማልችለው ስሜት አለ በሰውነቴ በእጄ ላይ ለሚፈጠሩት ጠባሳዎች ሀፍረት ይሰማኛል ነገር ግን በሌላ ቀን መልሼ አደርገዋለሁ ታውቂያለሽ እኔ ላስረዳው በማልችለው ነገር ተጎጂ ነኝ ግን እኔነቴን ማንም አያየውም የሆነ የተሰወረ ነገር አለ መሰለኝ እናም በቃ ህመሜን ማንም አያስተውልም እያንዳንዱ ሰው እኮ የማይናገረው የራሱ የሆኑ ችግሮችን ያልፋል እርስ በእርስ ደግ መሆን ቅን መሆን ያን ያህል ከባድ ነው እንዴ? በፊት ልጆች እያለን የሚያስጨንቀን እና የሚያሳዝነን ስሜቶችን ለማጠብ እንባዎቻችን ምቹ ነበሩ ፡፡ ስናድግ ግን የሆነ በጭራሽ በእንባ ሊታጠቡ የማይችሉ በጭራሽ መታጠብ ማይገባቸው የሚያሰቃዩ ትዝታዎች ፣በጣም የሚያሳዝዝኑ፣ የሚጎዱ፣ የሚሰብሩ፣ነገሮች እንዳሉ እንማራለን፡፡ ስለዚህ አንዳንዳንዶቻችን ማልቀስ ስንፈልግ እንስቃለን፣ማውራት እየፈለግን ዝም እንላለን፡፡ ዝም ብለን እየሳቅን ሁሉንም ህመምና ሀዘን እንቋቋማለን ሲበዛና ከአቅማችን በላይ ሲሆን ደሞ ራሳችንን ሱስ ውስጥ እንደብቃለን፡፡" ብላ ማልቀስ ጀመረች። ፍርዲ ልክ ናት ፍርዲ አዋቂ ናት ምትናገረው ነገር በሙሉ ልክ ነው ወላሂ በራሴ አዘንኩ፣ሰው መባሌ አስጠላኝ፣ አንገቴን አስደፋችኝ ከረጅም ዝምታ በኋላ የያዘችውን ያለቀ ሲጋራ ጥላ እጇን ጠራረገችና "ፍርዶውስ" አለችኝ ፈገግ ብዬ "ሰብሪን"አልኳት "ይቅርታ እንግዲህ ብሶቴን ተወጣውብሽ አንዳንዴ አዳማጭ ጆሮ ስታገኚ ገባሽ ደስ ይላል ብቻ አመሰግናለሁ ስላወቅኩሽ ደስ ብሎኛል"ብላ ፈገግ አለች"ፍርዲ እኔ አንቺን ከዚህ በላይ ማወቅ እፈልጋለው ስለራስሽ ብትነግሪኝ ደስ ይለኛል" ስላት "አየችኝ እና እርግጠኛ ነሽ ስለኔ መስማት ትፈልጊያለሽ" አለችኝ ውስጧ ላይ የተሰማት ደስታ ፊቷ ላይ ወጣ በጣም ብዙ ነገር መናገር እንደምትፈልግና እውነትም ጭንቀቷን ብሶቷን ሰምቶ ሸክሟን የሚያቀልላት ሰው እንደምትፈልግ ተረዳሁ "በደስታ ነዋ ለዛውም የምሰማሽ" ብዬ ፈገግ አልኩኝ.....ይቀጥላል