.......ሁለት ገፅታ....(ክፍል አራት)
(በኹሉድ ኑሪ)
"እሺ ከልጅነቴ ልጀምርልሽ እኔ የቤቱ ብቸኛ ልጅ ነኝ ተወልጄ 17 አመት እስኪሞላኝ ድረስ እንኖር የነበረው ሳር ቤት ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነበር ። ቤታችን ቤተመንግስት ነበር የሚመስለው በሰፈሩ የታወቅን ሃብታሞች ነበርን ። አባቴ በጣም ጎበዝ፣ታታሪ፣የሰው ሐቅ የማይነካ በሰዋች ና በስራ ባልደረባዎች ዘንድ ትልቅ ክብርና ፍቅር ያለው ሰው ነበር ። የሚገርምሽ አባቴ እንደ አንዳንድ ስግብግብ ሃብታሞች ራስ ወዳድ እና ከአላህ መንገድ የወጣ አነበረም እኔ እና እሱ መሐል ደግሞ የተለየ ፍቅር እና ከእናቴ የበለጠ ግንኙነት ነበረን ከእናቴ ጋር ግን ብዙም የጠበቀ ቅርበት አነበረንም ም/ም ደግሞ ከአባቴ ጋር ምክንያቱን ባላውቅም ሁሌ ቀን እና ማታ ስትጨቃጨቀው ሁሌም ስትጮህበት ነበር የማየው ለእኔም እንደ እናት አትቀርበኝም ነበር።እኔ ከአባቴ ውጪ እንደወንድም የምቀርበው አብረን ያደግነውን ኢምራንን ነበር ኢምራን ከኛ ቤት አጠገብ ይኖሩ የነበሩ የአባቴ ወንድም (የአጎቴ) ልጅ ነበር ከእኔ በ 2ዓመት ይበልጣል ። ኢምራን ሁሌም አብሮኝ ነበር ሚሆነው ለሱ የተለየ የወንድምነት ፍቅር ነበረኝ እሱም እንደዛው።አባቴ ከ10ዓመቴ በኋላ የግል ዑስታዝ ቀጠረልኝ ሁሌም ከ ቀለም ትምህርት ይበልጥ ወደ ዲን ትምህርት እንዳተኩር ነበር ግፊት ሚያደርግብኝ እኔም እሱ ነበር ፍላጎቴ እናም በ 13 አመቴ ነበር ኻፊዘል ቁርዐን የሆንኩት (ቁርዓኑን በቃሌ የያዝኩት) በ 17 ዓመቴ ደሞ የተለያዩ ኪታቦችን እና የቁርዓን ሙሉ ትርጉሞችን በቃሌ መሸምደድ ቻልኩኝ ያለ ማንም ግፊት በራሴ ፍላጎት ጅልባብ ለበስኩኝ። አባቴ እና እኔ ደስተኛ ብንሆንም እናቴ ግን የቀለም ትምህርቴ ላይ ትኩረት አለመስጠቴ ሁሌም ያበሳጫትና ከአባቴ ጋር ያጨቃጭቃት ነበር።አንድ ቀን አይቻቸው ማላውቃቸው ሰዎች ወደ ቤታችን መጥተው ለአባቴ እና ለእናቴ የሆነ ወረቀት ሰጥተዋቸው ሄዱ ወረቀቱን ሲቀበሉ አባቴ ምንም አልመሰለውም ነበር እናቴ ግን በድንጋጤ እጇ ተንቀጠቀጠ አባቴ ላይ በሃይለኛው መጮህ ጀመረች እንድትረጋጋ በቀስታ ቢነግራትም ምንም መረጋጋት አልቻለችም ምን እንደተፈጠረ ብጠይቃቸውም ምንም መልስ ሊሰጡኝ አልቻሉም በመጨረሻም እናቴ ጥላን ወደ ቤት ገብታ ሻንጣዋን ማዘጋጀት ጀመረች አባቴ ተከትሏት ገብቶ ተረጋግተው ቁጭ ብለው እንዲያወሩ ቢጠይቃትም ጆሮ ዳባ ብላ ሻንጣዋን እየጎተተች ወጣች እኔ እና አባቴ እየተከተልን ተማፀናት አባቴ እግሯ ላይ ወድቆ ሲለምናት ገፍትራው ጥላን ሄደች። አባቴ አሳዘነኝ ውስጤ በጣም ተሰበረ ተንበርክኬ ቤታችን ውስጥ የገባውን ሴጣን አላህ እንዲያወጣልን ዱዓ አደረኩኝ እናቴን እንዲመልስልኝ ተደፍቼ አለቀስኩኝ አባቴ ተነስቶ መጣ እና አቀፈኝ አንገቱ ውስጥ ተወሽቄ አለቀስኩ አባቴም እራሴን እንዳጠነክር እና ጎበዝ እንድሆን ሁሌም በአላህ ተስፋ እንዳልቆርጥ ነገረኝ ምን እንደተፈጠረ ስጠይቀው ከትንሽ ቀን በኋላ ይሄን ቤት ትተን እዚህ ሰፈር አከራይተነው የነበረው ማለት አሁን የምንኖርበት ቤት እንደምንሄድ ወደፊት ሁሉንም ነገር እንደምደርስበት ነገረኝ። ከትንሽ ቀናት በኋላ ቤቱን ለቀን እዚህ መጣን እናቴ ከሄደች በኋላ በቀን በቀን ይመጡ የነበሩት አጎቴ እና ኢምራን ድራሻቸው ጠፋ ስለ እናቴም ስለ እነሱም አንድም ነገር ሰምቼ አላውቅም ነበር አባቴም እሷ ጥላን ከሄደች ጀምሮ ምንም ጤንነት ተሰምቶት አያውቅም ሁሌም እራሴን ያመኛል ይለናል ብዙ ጊዜም ያዞረው ነበር።ከአንድ ዓመት በኋላ አባቴ የአልጋ ቁራኛ ሆነ እኔና አብራን ወደዚህ የመጣችው ኻዲማችን እሱን ለማሳከም ሆስፒታል ስንወስደው ዶክተሮቹ የአባቴ በሽታ የጭንቅላት ዕጢ እንደሆነና ባፋጣኝ ውጪ ሄዶ መታከም እንዳለበት ነገሩን ለሱም ብዙ ብር ተጠየቅን ነገር ግን ያሉንን ገንዘብ ማግኘት አልቻልንም ምክንያቱም ያለን ሙሉ ሃብት ተመናምኗል ያለንን ሁሉንም ነገሮች ሸጥን ሆኖም ዶክተሮቹ ያሉንን ገንዘብ ግማሹን እንኳ ማግኘት አልቻልንም አባቴ የሚያውቃቸው ለክፉ ቀን ለደረሰላቸው ሰዎች ሄጄ እያለቀስኩ ብለምናቸውም አብዛኛዎቹ ፊታቸውን አዞሩብኝ አንዳንዶቹ ግን ከ 2000 ብር በላይ ሊሰጡኝ አልቻሉም በመጨረሻም ወደ አጎቴ ጋር ሄድኩኝ እሱ ግን የለም አስብሎ ከውጪ መለሱኝ እናቴን ፍለጋም ብዙ ኳተንኩ ሆኖም ላገኛት አልቻልኩም የማረገው ግራ ገባኝ ያለንበት ቤት እንዲሸጥ ለአባቴ ብናማክረውም"በፍፁም ከሸጣችሁት አፉ አልላቹም" አለን አባቴን በገንዘብ ምክንያት ላጣው መሆኑ አንገበገበኝ ምነው ስቃዬን አበዛከው ብዬ ፈጣሪዬን አማረርኩ። አንድ ቀን ከአባቴ አጠገብ ቁጭ ብዬ ሳለው አንዲት ሴት ወደቤታችን ዘው ብላ ገባችና "አሰላሙ አለይኩም"አለች ድምጿ አዲስአልሆነብኝም እኔም አባቴም "ወአለይኪ ሰላም" ብለን ቀና ስንል እናቴ ናት በጣም ደነገጥኩኝ ወድያሁኑ አባቴን ሳየው በደስታ ፊቱ ፈክቷል "አልሃምዱሊላህ መጣሽልኝ ብሎ "ቀና ለማለት ሲሞክር ሮጣ ሄዳ አቀፈችው እና ማልቀስ ጀመረች እኔ ቆሜ እንባዬን እያፈሰስኩ አየዋቸው ከረጅም ደይቃ በኋላ አባቴ ነይ አለኝና አፉ እንድንባባል ጠየቀኝ በጣም ገረመኝ የት እንደሰነበተች እንኳን ሳይጠይቃት ስቆ ተቀበላት እኔም እሱን ላለማስከፋት እሺ ብዬ አቀፍኳት ግን ውስጤ ቂም ቋጥሮባታል ።አባቴ ያለበትን ነገር እንደሰማችና ነገሁኑ እንደምናሳክመው እየነገረችን አባቴ ማጣጣር ጀመረ ተደናግጠን ከበብነው "አባዬ አባዬ" ብለው አልሰማ አለኝ "ሁሉንም አፉ ብያለው አፉ በሉኝ ፍርዶውስን አደራ አደራ" ብሎ ሸኻዳ እየያዘ ሩኹ ወጣ። ሃዘኑ በጣም ጎዳኝ እናቴ የገደለችው እስኪመስለኝ ለዓይን አስጠላችኝ።ለቅሶ ላይ ብዙ ባለሀብቶች ተገኙ እነሱ ባለቀሱ ቁጥር እኔ በግርምት ስስቅ "ምፅ ይህች ልጅ ጭንቅላቷ ተነካ" እያሉ ይጠቋቆሙ ነበር።አጎት ተብዬ ግን በራችንን ረግጦት አያውቅም ነበር።ቀናቶች በሄዱ ቁጥር ቤታችንን የሞላው ሰው እየቀነሰ መጥቶ የሰፈር ሰዎች ብቻ ቀሩ ለምን እንደሆ ባላውቅም ሁሉም ይጠቋቆሙብኝ ነበር አንድ ቀን መንገድ ላይ እየሄድኩኝ ኢምራንን አገኘሁት "እንዴ ፍርዲ" ብሎ መጥቶ ተጠመጠመብኝ እኔም ከእላዬ ላይ ገፍትሬ እስካሁን የት እንደነበር ስጠይቀው ከቤት ተጣልቶ የራሱን ቤት ተከራይቶ እንደሚኖር ነገረኝ እና ቤቱን ካላሳየሁሽ አትሄጂም ብሎ ያዘኝ እኔም ተስማምቼ አብሬው ሄድኩኝ። ቤቱ ደስ ይላል ባለ ሁለት ክፍል ናት ነገር ግን ዝብርቅርቁ ወጥቷል "ምን ሆነክ ነው ምንድነው ሚመስለው ቤትክ ብዬ"ጅልባቤን አውልቄ ሳፀዳ በግርምት አየኝ እና"ፍርዲ ትልቅ ልጅ ሆንሻ እስካሁን ቤት መሆንሽ ይገርማል እኔ እኮ ቤተሰቦችሽ እንዳልሆኑ ካወቅሽ በኋላ አብረሻቸው ምትኖሪ አልመሰለኝም ነበር"ሲለኝ ሰውነቴን ነዘረኝ "ምንድነው ምቀባጥረው"ብዬ አፈጠጥኩበት "ምነው በሱ ምክንያት አደል እንዴ የተጣሉት እናትና አባትሽ አለኝ" ጅልባቤን እዛው ትቼው እየሮጥኩ ሄድኩ።ቤት ስገባ እናቴ ከሰፈር ሴቶች ጋር ነበረች ጎትቼ መኝታ ክፍል አስገባዎት እና "እናንተ አባትና እናቴ አደላችሁም?አዎ ወይ አይ በይኝ "ብዬ አፈጠጥኩባት በጣም ደነገጠች "ፍርዲ ምን መሰለሽ"ስትለኝ "ምንም አታስረጂኝ አዎ ወይ አይ በይ" ብዬ ጮህኩኝ ሁሉም ሰምቶ ወደኛ መጡ እናቴም "አዎ" አለችኝ በሩን በርግጄ ስወጣ እናቴ ከኋላ ተከትላ ስትይዘኝ ገፍትርያት ወጣው ሁሉ ነገር አስጠላኝ ሂጃቤን ጣልኩት በቲሸርት እና በሱሪ ብቻ ሆኜ እግሬ ወዳመራኝ ሄድኩ እምባዬ የለም በቃ ውስጤ ሲደማ ተሰማኝ ሁሉም ነገር አስጠላኝ ፈጣሪዬን ጠላቴ አደረኩት።አካባቢው ላይ የነበረው ግሮሰሪ ገባው እና ሰዎ
(በኹሉድ ኑሪ)
"እሺ ከልጅነቴ ልጀምርልሽ እኔ የቤቱ ብቸኛ ልጅ ነኝ ተወልጄ 17 አመት እስኪሞላኝ ድረስ እንኖር የነበረው ሳር ቤት ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነበር ። ቤታችን ቤተመንግስት ነበር የሚመስለው በሰፈሩ የታወቅን ሃብታሞች ነበርን ። አባቴ በጣም ጎበዝ፣ታታሪ፣የሰው ሐቅ የማይነካ በሰዋች ና በስራ ባልደረባዎች ዘንድ ትልቅ ክብርና ፍቅር ያለው ሰው ነበር ። የሚገርምሽ አባቴ እንደ አንዳንድ ስግብግብ ሃብታሞች ራስ ወዳድ እና ከአላህ መንገድ የወጣ አነበረም እኔ እና እሱ መሐል ደግሞ የተለየ ፍቅር እና ከእናቴ የበለጠ ግንኙነት ነበረን ከእናቴ ጋር ግን ብዙም የጠበቀ ቅርበት አነበረንም ም/ም ደግሞ ከአባቴ ጋር ምክንያቱን ባላውቅም ሁሌ ቀን እና ማታ ስትጨቃጨቀው ሁሌም ስትጮህበት ነበር የማየው ለእኔም እንደ እናት አትቀርበኝም ነበር።እኔ ከአባቴ ውጪ እንደወንድም የምቀርበው አብረን ያደግነውን ኢምራንን ነበር ኢምራን ከኛ ቤት አጠገብ ይኖሩ የነበሩ የአባቴ ወንድም (የአጎቴ) ልጅ ነበር ከእኔ በ 2ዓመት ይበልጣል ። ኢምራን ሁሌም አብሮኝ ነበር ሚሆነው ለሱ የተለየ የወንድምነት ፍቅር ነበረኝ እሱም እንደዛው።አባቴ ከ10ዓመቴ በኋላ የግል ዑስታዝ ቀጠረልኝ ሁሌም ከ ቀለም ትምህርት ይበልጥ ወደ ዲን ትምህርት እንዳተኩር ነበር ግፊት ሚያደርግብኝ እኔም እሱ ነበር ፍላጎቴ እናም በ 13 አመቴ ነበር ኻፊዘል ቁርዐን የሆንኩት (ቁርዓኑን በቃሌ የያዝኩት) በ 17 ዓመቴ ደሞ የተለያዩ ኪታቦችን እና የቁርዓን ሙሉ ትርጉሞችን በቃሌ መሸምደድ ቻልኩኝ ያለ ማንም ግፊት በራሴ ፍላጎት ጅልባብ ለበስኩኝ። አባቴ እና እኔ ደስተኛ ብንሆንም እናቴ ግን የቀለም ትምህርቴ ላይ ትኩረት አለመስጠቴ ሁሌም ያበሳጫትና ከአባቴ ጋር ያጨቃጭቃት ነበር።አንድ ቀን አይቻቸው ማላውቃቸው ሰዎች ወደ ቤታችን መጥተው ለአባቴ እና ለእናቴ የሆነ ወረቀት ሰጥተዋቸው ሄዱ ወረቀቱን ሲቀበሉ አባቴ ምንም አልመሰለውም ነበር እናቴ ግን በድንጋጤ እጇ ተንቀጠቀጠ አባቴ ላይ በሃይለኛው መጮህ ጀመረች እንድትረጋጋ በቀስታ ቢነግራትም ምንም መረጋጋት አልቻለችም ምን እንደተፈጠረ ብጠይቃቸውም ምንም መልስ ሊሰጡኝ አልቻሉም በመጨረሻም እናቴ ጥላን ወደ ቤት ገብታ ሻንጣዋን ማዘጋጀት ጀመረች አባቴ ተከትሏት ገብቶ ተረጋግተው ቁጭ ብለው እንዲያወሩ ቢጠይቃትም ጆሮ ዳባ ብላ ሻንጣዋን እየጎተተች ወጣች እኔ እና አባቴ እየተከተልን ተማፀናት አባቴ እግሯ ላይ ወድቆ ሲለምናት ገፍትራው ጥላን ሄደች። አባቴ አሳዘነኝ ውስጤ በጣም ተሰበረ ተንበርክኬ ቤታችን ውስጥ የገባውን ሴጣን አላህ እንዲያወጣልን ዱዓ አደረኩኝ እናቴን እንዲመልስልኝ ተደፍቼ አለቀስኩኝ አባቴ ተነስቶ መጣ እና አቀፈኝ አንገቱ ውስጥ ተወሽቄ አለቀስኩ አባቴም እራሴን እንዳጠነክር እና ጎበዝ እንድሆን ሁሌም በአላህ ተስፋ እንዳልቆርጥ ነገረኝ ምን እንደተፈጠረ ስጠይቀው ከትንሽ ቀን በኋላ ይሄን ቤት ትተን እዚህ ሰፈር አከራይተነው የነበረው ማለት አሁን የምንኖርበት ቤት እንደምንሄድ ወደፊት ሁሉንም ነገር እንደምደርስበት ነገረኝ። ከትንሽ ቀናት በኋላ ቤቱን ለቀን እዚህ መጣን እናቴ ከሄደች በኋላ በቀን በቀን ይመጡ የነበሩት አጎቴ እና ኢምራን ድራሻቸው ጠፋ ስለ እናቴም ስለ እነሱም አንድም ነገር ሰምቼ አላውቅም ነበር አባቴም እሷ ጥላን ከሄደች ጀምሮ ምንም ጤንነት ተሰምቶት አያውቅም ሁሌም እራሴን ያመኛል ይለናል ብዙ ጊዜም ያዞረው ነበር።ከአንድ ዓመት በኋላ አባቴ የአልጋ ቁራኛ ሆነ እኔና አብራን ወደዚህ የመጣችው ኻዲማችን እሱን ለማሳከም ሆስፒታል ስንወስደው ዶክተሮቹ የአባቴ በሽታ የጭንቅላት ዕጢ እንደሆነና ባፋጣኝ ውጪ ሄዶ መታከም እንዳለበት ነገሩን ለሱም ብዙ ብር ተጠየቅን ነገር ግን ያሉንን ገንዘብ ማግኘት አልቻልንም ምክንያቱም ያለን ሙሉ ሃብት ተመናምኗል ያለንን ሁሉንም ነገሮች ሸጥን ሆኖም ዶክተሮቹ ያሉንን ገንዘብ ግማሹን እንኳ ማግኘት አልቻልንም አባቴ የሚያውቃቸው ለክፉ ቀን ለደረሰላቸው ሰዎች ሄጄ እያለቀስኩ ብለምናቸውም አብዛኛዎቹ ፊታቸውን አዞሩብኝ አንዳንዶቹ ግን ከ 2000 ብር በላይ ሊሰጡኝ አልቻሉም በመጨረሻም ወደ አጎቴ ጋር ሄድኩኝ እሱ ግን የለም አስብሎ ከውጪ መለሱኝ እናቴን ፍለጋም ብዙ ኳተንኩ ሆኖም ላገኛት አልቻልኩም የማረገው ግራ ገባኝ ያለንበት ቤት እንዲሸጥ ለአባቴ ብናማክረውም"በፍፁም ከሸጣችሁት አፉ አልላቹም" አለን አባቴን በገንዘብ ምክንያት ላጣው መሆኑ አንገበገበኝ ምነው ስቃዬን አበዛከው ብዬ ፈጣሪዬን አማረርኩ። አንድ ቀን ከአባቴ አጠገብ ቁጭ ብዬ ሳለው አንዲት ሴት ወደቤታችን ዘው ብላ ገባችና "አሰላሙ አለይኩም"አለች ድምጿ አዲስአልሆነብኝም እኔም አባቴም "ወአለይኪ ሰላም" ብለን ቀና ስንል እናቴ ናት በጣም ደነገጥኩኝ ወድያሁኑ አባቴን ሳየው በደስታ ፊቱ ፈክቷል "አልሃምዱሊላህ መጣሽልኝ ብሎ "ቀና ለማለት ሲሞክር ሮጣ ሄዳ አቀፈችው እና ማልቀስ ጀመረች እኔ ቆሜ እንባዬን እያፈሰስኩ አየዋቸው ከረጅም ደይቃ በኋላ አባቴ ነይ አለኝና አፉ እንድንባባል ጠየቀኝ በጣም ገረመኝ የት እንደሰነበተች እንኳን ሳይጠይቃት ስቆ ተቀበላት እኔም እሱን ላለማስከፋት እሺ ብዬ አቀፍኳት ግን ውስጤ ቂም ቋጥሮባታል ።አባቴ ያለበትን ነገር እንደሰማችና ነገሁኑ እንደምናሳክመው እየነገረችን አባቴ ማጣጣር ጀመረ ተደናግጠን ከበብነው "አባዬ አባዬ" ብለው አልሰማ አለኝ "ሁሉንም አፉ ብያለው አፉ በሉኝ ፍርዶውስን አደራ አደራ" ብሎ ሸኻዳ እየያዘ ሩኹ ወጣ። ሃዘኑ በጣም ጎዳኝ እናቴ የገደለችው እስኪመስለኝ ለዓይን አስጠላችኝ።ለቅሶ ላይ ብዙ ባለሀብቶች ተገኙ እነሱ ባለቀሱ ቁጥር እኔ በግርምት ስስቅ "ምፅ ይህች ልጅ ጭንቅላቷ ተነካ" እያሉ ይጠቋቆሙ ነበር።አጎት ተብዬ ግን በራችንን ረግጦት አያውቅም ነበር።ቀናቶች በሄዱ ቁጥር ቤታችንን የሞላው ሰው እየቀነሰ መጥቶ የሰፈር ሰዎች ብቻ ቀሩ ለምን እንደሆ ባላውቅም ሁሉም ይጠቋቆሙብኝ ነበር አንድ ቀን መንገድ ላይ እየሄድኩኝ ኢምራንን አገኘሁት "እንዴ ፍርዲ" ብሎ መጥቶ ተጠመጠመብኝ እኔም ከእላዬ ላይ ገፍትሬ እስካሁን የት እንደነበር ስጠይቀው ከቤት ተጣልቶ የራሱን ቤት ተከራይቶ እንደሚኖር ነገረኝ እና ቤቱን ካላሳየሁሽ አትሄጂም ብሎ ያዘኝ እኔም ተስማምቼ አብሬው ሄድኩኝ። ቤቱ ደስ ይላል ባለ ሁለት ክፍል ናት ነገር ግን ዝብርቅርቁ ወጥቷል "ምን ሆነክ ነው ምንድነው ሚመስለው ቤትክ ብዬ"ጅልባቤን አውልቄ ሳፀዳ በግርምት አየኝ እና"ፍርዲ ትልቅ ልጅ ሆንሻ እስካሁን ቤት መሆንሽ ይገርማል እኔ እኮ ቤተሰቦችሽ እንዳልሆኑ ካወቅሽ በኋላ አብረሻቸው ምትኖሪ አልመሰለኝም ነበር"ሲለኝ ሰውነቴን ነዘረኝ "ምንድነው ምቀባጥረው"ብዬ አፈጠጥኩበት "ምነው በሱ ምክንያት አደል እንዴ የተጣሉት እናትና አባትሽ አለኝ" ጅልባቤን እዛው ትቼው እየሮጥኩ ሄድኩ።ቤት ስገባ እናቴ ከሰፈር ሴቶች ጋር ነበረች ጎትቼ መኝታ ክፍል አስገባዎት እና "እናንተ አባትና እናቴ አደላችሁም?አዎ ወይ አይ በይኝ "ብዬ አፈጠጥኩባት በጣም ደነገጠች "ፍርዲ ምን መሰለሽ"ስትለኝ "ምንም አታስረጂኝ አዎ ወይ አይ በይ" ብዬ ጮህኩኝ ሁሉም ሰምቶ ወደኛ መጡ እናቴም "አዎ" አለችኝ በሩን በርግጄ ስወጣ እናቴ ከኋላ ተከትላ ስትይዘኝ ገፍትርያት ወጣው ሁሉ ነገር አስጠላኝ ሂጃቤን ጣልኩት በቲሸርት እና በሱሪ ብቻ ሆኜ እግሬ ወዳመራኝ ሄድኩ እምባዬ የለም በቃ ውስጤ ሲደማ ተሰማኝ ሁሉም ነገር አስጠላኝ ፈጣሪዬን ጠላቴ አደረኩት።አካባቢው ላይ የነበረው ግሮሰሪ ገባው እና ሰዎ