ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤን በተሳካ መልኩ እያስተናገደች ነው -የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
************************
ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤን በተሳካ መልኩ እያስተናገደች መሆኑን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ገለጸ።
የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ 38ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤን አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ በ46ኛው የአፍሪካ ሕብረት የስራ አስፈጻሚዎች ስብሰባ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሕብረት የሰላም እና ጸጥታ ምክር ቤት አባል ሆና መመረጧ ትልቅ ስኬት መሆኑን ገልፀዋል።
ኢትዮጵያ 38ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ ተሳታፊዎችን በክብር ተቀብላ እያስተናገደች መሆኑን የገለፁት ሚኒስትር ዴኤታው ኢትዮጵያ እንግዶችን ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ጀምሮ በከፍተኛ የመንግሥት ኃላፊዎች አቀባበል ማድረጓን አንስተዋል።
ሚኒስትር ዴኤታው በሕብረቱ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያ ለፓን አፍሪካኒዝም እሳቤ መጎልበት እንዲሁም ለአፍሪካ ሕብረት መጠናከር ጉልህ ሚና ማበርከቷንና ይህንን አጠናክራ እንደምትቀጥል ማንሳታቸውን ገልጸዋል።
በተለይ እርስ በእርስ የተባበረና በመሰረተ ልማት የተሳሰረ አህጉር ለመፍጠር ከሌሎች ውንድም እና እህት አፍሪካውያን ጋር እንደምትሰራ እንዲሁም በግብርናው ዘርፍ ያስመዘገበችው ውጤት ለአፍሪካውያን ምሳሌ እንደሚሆን መግለጻቸውንም ጠቅሰዋል፡፡
************************
ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤን በተሳካ መልኩ እያስተናገደች መሆኑን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ገለጸ።
የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ 38ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤን አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ በ46ኛው የአፍሪካ ሕብረት የስራ አስፈጻሚዎች ስብሰባ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሕብረት የሰላም እና ጸጥታ ምክር ቤት አባል ሆና መመረጧ ትልቅ ስኬት መሆኑን ገልፀዋል።
ኢትዮጵያ 38ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ ተሳታፊዎችን በክብር ተቀብላ እያስተናገደች መሆኑን የገለፁት ሚኒስትር ዴኤታው ኢትዮጵያ እንግዶችን ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ጀምሮ በከፍተኛ የመንግሥት ኃላፊዎች አቀባበል ማድረጓን አንስተዋል።
ሚኒስትር ዴኤታው በሕብረቱ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያ ለፓን አፍሪካኒዝም እሳቤ መጎልበት እንዲሁም ለአፍሪካ ሕብረት መጠናከር ጉልህ ሚና ማበርከቷንና ይህንን አጠናክራ እንደምትቀጥል ማንሳታቸውን ገልጸዋል።
በተለይ እርስ በእርስ የተባበረና በመሰረተ ልማት የተሳሰረ አህጉር ለመፍጠር ከሌሎች ውንድም እና እህት አፍሪካውያን ጋር እንደምትሰራ እንዲሁም በግብርናው ዘርፍ ያስመዘገበችው ውጤት ለአፍሪካውያን ምሳሌ እንደሚሆን መግለጻቸውንም ጠቅሰዋል፡፡