መንግስታዊዉ ባንክ የሆነዉ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በኢንዱስትሪው ያለዉ የገበያ ድርሻ ቀነሰ
ግዙፉ የፋይናንስ ተቋም የሆነዉ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በባንክ ኢንዱስትሪው ላይ ያለዉ የገበያ ድርሻ ካለፈዉ ዓመት አኳያ ቅናሽ ማሳየቱ አዲሱ የብሔራዊ ባንክ ሪፖርት አመላክቷል።
ባንኩ በ 2016 ሂሳብ ዓመት አጠቃላይ ሀብቱ እና የተቀማጭ ገንዘብ ከጠቅላላው የባንክ ዘርፍ ከግማሽ በታች ማለትም 47.9 በመቶ እና 47.1 በመቶ በቅደም ተከተል መሆኑን ተመላክቷል።
ይህም ባንኩ በ 2015 የነበረዉ ድርሻ ከባንክ ኢንዱስትሪው አጠቃላይ ሀብቱ 49.5 በመቶ የነበረ ሲሆን ተቀማጭ ገንዘብ ደግሞ 48.7 በመቶ መሆኑ ይታወቃል።
ብሔራዊ ባንክ በተጠናቀቀዉ ሂሳብ ዓመት የባንክ ኢንዱስትሪ የገበያ ድርሻ በሚመለከት ትልቅ ፣ መካከለኛ እና አነስተኛ በሚል በአፈፃፀማቸዉ ልክ አስቀምጧል።
በዓመቱ የገበያ ድርሻዉ ምንም እንኳን ዝቅተኛ ቢሆንም አሁንም በሀገሪቱ ከሚገኙ ባንኮች ትልቁን ድርሻ የያዘው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ነዉ።
እንደ ብሔራዊ ባንክ መረጃ አዋሽ ፣ አቢሲኒያ ፣ ዳሽን ፣ ኦሮሚያ እና ህብረት ባንክ መካከለኛ ባንኮች ተብለዉ ከተለዩ አምስቱ ተቋማቶች ሲሆኑ አጠቃላይ ሀብታቸው 28.9 በመቶ እና ተቀማጭ ገንዘባቸው ደግሞ 30.3 በመቶ መሆኑ ተገልጿል።
የተቀሩት 25 አነስተኛ ባንኮች ጥምር ንብረቶች እና ተቀማጭ ገንዘብ 23.3 በመቶ እና 22.7 በመቶ ድርሻ የያዙ ሲሆን ይህም ከአጠቃላይ የባንክ ዘርፍ እያንዳንዳቸው 0.8 በመቶ ጭማሪ ማሳየታቸውን ካፒታል ከሪፖርቱ ተመልክቷል።
Source: capitalethiopia
@Ethiopianbusinessdaily
ግዙፉ የፋይናንስ ተቋም የሆነዉ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በባንክ ኢንዱስትሪው ላይ ያለዉ የገበያ ድርሻ ካለፈዉ ዓመት አኳያ ቅናሽ ማሳየቱ አዲሱ የብሔራዊ ባንክ ሪፖርት አመላክቷል።
ባንኩ በ 2016 ሂሳብ ዓመት አጠቃላይ ሀብቱ እና የተቀማጭ ገንዘብ ከጠቅላላው የባንክ ዘርፍ ከግማሽ በታች ማለትም 47.9 በመቶ እና 47.1 በመቶ በቅደም ተከተል መሆኑን ተመላክቷል።
ይህም ባንኩ በ 2015 የነበረዉ ድርሻ ከባንክ ኢንዱስትሪው አጠቃላይ ሀብቱ 49.5 በመቶ የነበረ ሲሆን ተቀማጭ ገንዘብ ደግሞ 48.7 በመቶ መሆኑ ይታወቃል።
ብሔራዊ ባንክ በተጠናቀቀዉ ሂሳብ ዓመት የባንክ ኢንዱስትሪ የገበያ ድርሻ በሚመለከት ትልቅ ፣ መካከለኛ እና አነስተኛ በሚል በአፈፃፀማቸዉ ልክ አስቀምጧል።
በዓመቱ የገበያ ድርሻዉ ምንም እንኳን ዝቅተኛ ቢሆንም አሁንም በሀገሪቱ ከሚገኙ ባንኮች ትልቁን ድርሻ የያዘው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ነዉ።
እንደ ብሔራዊ ባንክ መረጃ አዋሽ ፣ አቢሲኒያ ፣ ዳሽን ፣ ኦሮሚያ እና ህብረት ባንክ መካከለኛ ባንኮች ተብለዉ ከተለዩ አምስቱ ተቋማቶች ሲሆኑ አጠቃላይ ሀብታቸው 28.9 በመቶ እና ተቀማጭ ገንዘባቸው ደግሞ 30.3 በመቶ መሆኑ ተገልጿል።
የተቀሩት 25 አነስተኛ ባንኮች ጥምር ንብረቶች እና ተቀማጭ ገንዘብ 23.3 በመቶ እና 22.7 በመቶ ድርሻ የያዙ ሲሆን ይህም ከአጠቃላይ የባንክ ዘርፍ እያንዳንዳቸው 0.8 በመቶ ጭማሪ ማሳየታቸውን ካፒታል ከሪፖርቱ ተመልክቷል።
Source: capitalethiopia
@Ethiopianbusinessdaily