በጋምቤላ ክልል በወረርሽኝ የዘጠኝ ሰዎች ህይወት አለፈ
የጋምቤላ ክልል የጤና ቢሮ የህብረተሰብ ጤና ዳይሬክተር አቶ ኝኪዎ ጊሎ እንደተናገሩት፤ለክልሉ አጎራባች በሆነው ደቡብ ሱዳን በሽታው ተከስቶ እንደነበር ተናግረዋል።
በክልሉ ኑዌር ብሔረሰብ ዞን በአኮቦ፣ ዋንቱዋ፣ ማኩዌይ እና ላሬ ወረዳዎች የአጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት መከሰቱን እና ኮሌራ መሆኑን ለማረጋገጥ ዉጤቱ እየተጠበቀ መሆኑን ገልጸዋል።
በበሽታው ከተያዙት 1መቶ36 ሰዎች መካከል የዘጠኝ ሰዎች ህይወት ሲያልፍ፤31 ሰዎች በህክምና ላይ እንደሚገኙም ነዉ አቶ ኝኪዎ የገለጹት፡፡
96 ሰዎች ደግሞ ከበሽታው ማገገማቸውንም ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡
የጋምቤላ ክልል የጤና ቢሮ የህብረተሰብ ጤና ዳይሬክተር አቶ ኝኪዎ ጊሎ እንደተናገሩት፤ለክልሉ አጎራባች በሆነው ደቡብ ሱዳን በሽታው ተከስቶ እንደነበር ተናግረዋል።
በክልሉ ኑዌር ብሔረሰብ ዞን በአኮቦ፣ ዋንቱዋ፣ ማኩዌይ እና ላሬ ወረዳዎች የአጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት መከሰቱን እና ኮሌራ መሆኑን ለማረጋገጥ ዉጤቱ እየተጠበቀ መሆኑን ገልጸዋል።
በበሽታው ከተያዙት 1መቶ36 ሰዎች መካከል የዘጠኝ ሰዎች ህይወት ሲያልፍ፤31 ሰዎች በህክምና ላይ እንደሚገኙም ነዉ አቶ ኝኪዎ የገለጹት፡፡
96 ሰዎች ደግሞ ከበሽታው ማገገማቸውንም ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡