ሰበር ዜና!
17 ሙትና 29 ቁስለኛ ሁኗል፤ አሁንም በከበባ ውስጥ ይገኛል!
የአማራ ፋኖ በወሎ በቀጠለው የህልዉና ተጋድሎ ላስታ አሳምነው ኮር ተከዜ ክፍለጦር እና ጥራሪ ክፍለጦር በጋራ ባደረጉት ተጋድሎ ታላቅ ድል ተጎናፅፈዋል::
ላስታ አሳምነው ኮር ከተቆጣጠራቸው አካባቢዎች አንዱ በሆነው ኩልመስክ ቀጠና ለማጥቃት ሶስት ሬጅመንት ከመካናይዝድ ጋር ያሰለፈው የአብይ አህመድ ዙፋን ጠባቂ ሰራዊት በፋኖ ኮማንዶ ዘላለም ሲሳይ የሚመራው ተከዜ ክፍለጦርና በአርበኛ ሻለቃ ብርሃን አሰፋ የሚመራው ጥራሪ ክፍለጦር ባደረጉት ብርቱ ትንቅንቅና ተጋድሎ በርካታ ሙትና ቁስለኛዉን ይዞ የተመለሰ ሲሆን ጠላት አሁንም ኩልመስክ ላይ ተከቦ ይገኛል::
ከራያ ቆቦ ተኩለሽና አካባቢው በበርካታ ተደጋጋሚ የደፈጣ ጥቃት ተሰላችቶና መፈናፈኛ አጥቶ ወደ ጊዳን ወረዳና ኩልመስክ የገባው ጠላት ቀጠናዉን ከአመት በላይ ተቆጣጥረው በሚገኙት የላስታ አሳምነው ኮር አሃዶች ጥራሪ ክፍለጦርና ተከዜ ክፍለጦር ተቀብለው እያስተናገዱት ይገኛሉ::
ኩልመስክና ሃሙሲት አካባቢ በተደረገው ጠንካራ ዉጊያ የጠላት ሰራዊት የተረፈረፈ ሲሆን 17 ሙትና 29 ቁስለኛ ሁኗል፤ ቀሪው የጠላት ኃይልም ኩልመስክ ላይ ከበባ ውስጥ ገብቶ እጅ ስጥ እየተባለ ይገኛል፤ ተጋድሎው ታህሳስ 18/2017 ዓ.ም ንጋት ጀምሮ እስከ ምሽት 1:00 ድረስ በጀግኖቹ ተከዜ ክፍለጦር እና ጥራሪ ክፍለጦር ትንቅንቅ የቀጠለ ሲሆን አሁንም የገባው ጠላት በማይወጣበት ሁኔታ ተከቦ ይገኛል::
ቅዱስ ላሊበላ ከተማና ቀጠናው ላይ ፖለቲካዊና ወታደራዊ ድል ለማግኘት የቋመጠው የምርኮኛው ብርሃኑ ጁላ ጦር በተለያየ አቅጣጫ ወደ ቅዱስ ላሊበላ ከተማ ሬሽን ለማስገባት ቢሞክርም የአማራ ፋኖ በወሎ ዋና አዛዥ ዋርካው ምሬ ወዳጆ በሰጠው ትዕዛዝ መሰረት በመጣበት አቅጣጫ ሁሉ እንደ እባብ እየተቀጠቀጠና እየተደመሰሰ ይገኛል ሲል የአማራ ፋኖ በወሎ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ገልጿል።
17 ሙትና 29 ቁስለኛ ሁኗል፤ አሁንም በከበባ ውስጥ ይገኛል!
የአማራ ፋኖ በወሎ በቀጠለው የህልዉና ተጋድሎ ላስታ አሳምነው ኮር ተከዜ ክፍለጦር እና ጥራሪ ክፍለጦር በጋራ ባደረጉት ተጋድሎ ታላቅ ድል ተጎናፅፈዋል::
ላስታ አሳምነው ኮር ከተቆጣጠራቸው አካባቢዎች አንዱ በሆነው ኩልመስክ ቀጠና ለማጥቃት ሶስት ሬጅመንት ከመካናይዝድ ጋር ያሰለፈው የአብይ አህመድ ዙፋን ጠባቂ ሰራዊት በፋኖ ኮማንዶ ዘላለም ሲሳይ የሚመራው ተከዜ ክፍለጦርና በአርበኛ ሻለቃ ብርሃን አሰፋ የሚመራው ጥራሪ ክፍለጦር ባደረጉት ብርቱ ትንቅንቅና ተጋድሎ በርካታ ሙትና ቁስለኛዉን ይዞ የተመለሰ ሲሆን ጠላት አሁንም ኩልመስክ ላይ ተከቦ ይገኛል::
ከራያ ቆቦ ተኩለሽና አካባቢው በበርካታ ተደጋጋሚ የደፈጣ ጥቃት ተሰላችቶና መፈናፈኛ አጥቶ ወደ ጊዳን ወረዳና ኩልመስክ የገባው ጠላት ቀጠናዉን ከአመት በላይ ተቆጣጥረው በሚገኙት የላስታ አሳምነው ኮር አሃዶች ጥራሪ ክፍለጦርና ተከዜ ክፍለጦር ተቀብለው እያስተናገዱት ይገኛሉ::
ኩልመስክና ሃሙሲት አካባቢ በተደረገው ጠንካራ ዉጊያ የጠላት ሰራዊት የተረፈረፈ ሲሆን 17 ሙትና 29 ቁስለኛ ሁኗል፤ ቀሪው የጠላት ኃይልም ኩልመስክ ላይ ከበባ ውስጥ ገብቶ እጅ ስጥ እየተባለ ይገኛል፤ ተጋድሎው ታህሳስ 18/2017 ዓ.ም ንጋት ጀምሮ እስከ ምሽት 1:00 ድረስ በጀግኖቹ ተከዜ ክፍለጦር እና ጥራሪ ክፍለጦር ትንቅንቅ የቀጠለ ሲሆን አሁንም የገባው ጠላት በማይወጣበት ሁኔታ ተከቦ ይገኛል::
ቅዱስ ላሊበላ ከተማና ቀጠናው ላይ ፖለቲካዊና ወታደራዊ ድል ለማግኘት የቋመጠው የምርኮኛው ብርሃኑ ጁላ ጦር በተለያየ አቅጣጫ ወደ ቅዱስ ላሊበላ ከተማ ሬሽን ለማስገባት ቢሞክርም የአማራ ፋኖ በወሎ ዋና አዛዥ ዋርካው ምሬ ወዳጆ በሰጠው ትዕዛዝ መሰረት በመጣበት አቅጣጫ ሁሉ እንደ እባብ እየተቀጠቀጠና እየተደመሰሰ ይገኛል ሲል የአማራ ፋኖ በወሎ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ገልጿል።