ስለሁሉም አመስግኑ!
ስለሆነው ስለሚሆነው ስለማይሆነው፣ ስላጣናቸው ስላገኘናቸው ፈልገንም ስላላገኘናቸው ስለተሰጠን ስለሚሰጠን፣ ስለማይሰጠን፣ ስላልተሳካልን ስለተሳካልን፣ ስለከሰርነው ስላተረፍነው ነገር በሙሉ ፈጣሪ ይመስገን። ስለሔደው በማልቀስ፣ ስለሚመጣውም በመጨነቅ ጊዜ ማጥፋት አያስፈልግም። ሁሉ ለበጎ ሁሉ ለመልካም እንደሚደረግ ማመን ከሁሉ ነገር ነፃ ያወጣል። ስለእራሳችን በሚገባ የምናውቅ ሊመስለን ይችላል ለእኛ የሚበጀንን ግን ከእኛ በተሻለ እግዚአብሔር አምላካችን እንደሚያውቅ ማስታወስ ያስፈልጋል። በህይወታችን የሚከሰቱ እያንዳንዱ ነገሮች በምክንያት የሚፈጠሩ ናቸው። ወደዳችሁም ጠላችሁም ከትናንት ጥፋታችሁና ከዛሬ ተግባራችሁ ጀርባ በቂ ምክንያት ነበረ፣ አለም።
አዎ! ጀግናዬ..! ስለሁሉም ምስጋና ይገባልና ምስጋናን አትሰስት፣ ነገሮች ሁሉ ለበጎ እንደሆኑ ለማሰብ ብዙ አትቸገር። ቅዱስ መፅሐፍ ይህን ይላል፦ "እግዚአብሔርንም ለሚወዱት እንደ ሃሳቡም ለተጠሩት ነገር ሁሉ ለበጎ እንዲደረግ እናውቃለን፡፡" ምንም ክፉ ነገር ቢከሰትብን፣ ምንም ለጊዜው የሚያሸማቅቅና አንገት የሚያስደፋ ሁነት ውስጥ ብንገኘ ሁኔታው ነገ ምን ይዞ እንደሚመጣ አናውቅምና ለበጎ እንደሆነ ማሰቡ ብዙ በረከትን ይዞልን ይመጣል። በማጣት ውስጥ መረጋጋት፣ በማግኘት ውስጥ መረጋጋት። በችግር መሃል ማመስገኛ ምክንያት መፈለግ፣ በደስታ መሃልም እንዲሁ ምስጋናን ማስቀደም ተገቢ ነው። በማማረር የሚገኝ ነገር ቢኖር ሌላ ተጨማሪ የሚያማርር ነገር ነው፤ ከማመስገንም እንዲሁ ሌላ ማመስገኛ ነገር ነው። በረከትን በመቁጠር ሌላ በረከት ይገኛል፣ እርግማንን ደጋግሞ በማሰብም እንዲሁ ተጨማሪ ችግርን ወደእራሳችን እንጠራለን።
አዎ! ፈጣሪን የምታመሰግኑት ሁሉን የሚያደርግላችሁ እርሱ ስለሆነ ነው፤ ሰዎችን የምታበረታቱት፣ ሰዎችን የምታደንቁት ብሎም ደስተኛ እንዲሆኑ የምትጥሩት እናንተም ይሔ ነገር እንዲደረግላችሁ በምትፈልጉት መጠን ነው። ክፉ ሰው መልካም ነገር ከሰዎች አይጠብቅም፤ ውሸታም ሰው ማንም እውነት የሚያወራ አይመስለውም፤ አቃቂር በማውጣት የተጠመደ ሰው ምንም በጎ ስራ አይታየውም። ከእናንተ የተሻለ ህይወት የሚኖሩ የሚመስሏችሁን ሰዎች እየተመለከታችሁ ከአመስጋኝነት አትራቁ፣ የሌላችሁን እየቆጠራችሁ ለጭንቀትና ለብቸኝነት እራሳችሁን አታጋልጡ። እያንዳንዱ ችላ የምትሉት ትንሽ ልማዳችሁ እያደር ዋጋ እንደሚያስከፍላችሁ አትርሱ። ከምስጋና የራቀ ሰው ከታሰበለት በረከቱም እንዲሁ እየራቀ ይሔዳል። ስለሁሉም አመስግኑ፣ እለት እለት በልባዊ ምስጋና ውስጣችሁን አድሱ፣ በረከታችሁን ጨምሩ፣ ደስታችሁንም እራሳችሁ ፍጠሩት።
ስለሆነው ስለሚሆነው ስለማይሆነው፣ ስላጣናቸው ስላገኘናቸው ፈልገንም ስላላገኘናቸው ስለተሰጠን ስለሚሰጠን፣ ስለማይሰጠን፣ ስላልተሳካልን ስለተሳካልን፣ ስለከሰርነው ስላተረፍነው ነገር በሙሉ ፈጣሪ ይመስገን። ስለሔደው በማልቀስ፣ ስለሚመጣውም በመጨነቅ ጊዜ ማጥፋት አያስፈልግም። ሁሉ ለበጎ ሁሉ ለመልካም እንደሚደረግ ማመን ከሁሉ ነገር ነፃ ያወጣል። ስለእራሳችን በሚገባ የምናውቅ ሊመስለን ይችላል ለእኛ የሚበጀንን ግን ከእኛ በተሻለ እግዚአብሔር አምላካችን እንደሚያውቅ ማስታወስ ያስፈልጋል። በህይወታችን የሚከሰቱ እያንዳንዱ ነገሮች በምክንያት የሚፈጠሩ ናቸው። ወደዳችሁም ጠላችሁም ከትናንት ጥፋታችሁና ከዛሬ ተግባራችሁ ጀርባ በቂ ምክንያት ነበረ፣ አለም።
አዎ! ጀግናዬ..! ስለሁሉም ምስጋና ይገባልና ምስጋናን አትሰስት፣ ነገሮች ሁሉ ለበጎ እንደሆኑ ለማሰብ ብዙ አትቸገር። ቅዱስ መፅሐፍ ይህን ይላል፦ "እግዚአብሔርንም ለሚወዱት እንደ ሃሳቡም ለተጠሩት ነገር ሁሉ ለበጎ እንዲደረግ እናውቃለን፡፡" ምንም ክፉ ነገር ቢከሰትብን፣ ምንም ለጊዜው የሚያሸማቅቅና አንገት የሚያስደፋ ሁነት ውስጥ ብንገኘ ሁኔታው ነገ ምን ይዞ እንደሚመጣ አናውቅምና ለበጎ እንደሆነ ማሰቡ ብዙ በረከትን ይዞልን ይመጣል። በማጣት ውስጥ መረጋጋት፣ በማግኘት ውስጥ መረጋጋት። በችግር መሃል ማመስገኛ ምክንያት መፈለግ፣ በደስታ መሃልም እንዲሁ ምስጋናን ማስቀደም ተገቢ ነው። በማማረር የሚገኝ ነገር ቢኖር ሌላ ተጨማሪ የሚያማርር ነገር ነው፤ ከማመስገንም እንዲሁ ሌላ ማመስገኛ ነገር ነው። በረከትን በመቁጠር ሌላ በረከት ይገኛል፣ እርግማንን ደጋግሞ በማሰብም እንዲሁ ተጨማሪ ችግርን ወደእራሳችን እንጠራለን።
አዎ! ፈጣሪን የምታመሰግኑት ሁሉን የሚያደርግላችሁ እርሱ ስለሆነ ነው፤ ሰዎችን የምታበረታቱት፣ ሰዎችን የምታደንቁት ብሎም ደስተኛ እንዲሆኑ የምትጥሩት እናንተም ይሔ ነገር እንዲደረግላችሁ በምትፈልጉት መጠን ነው። ክፉ ሰው መልካም ነገር ከሰዎች አይጠብቅም፤ ውሸታም ሰው ማንም እውነት የሚያወራ አይመስለውም፤ አቃቂር በማውጣት የተጠመደ ሰው ምንም በጎ ስራ አይታየውም። ከእናንተ የተሻለ ህይወት የሚኖሩ የሚመስሏችሁን ሰዎች እየተመለከታችሁ ከአመስጋኝነት አትራቁ፣ የሌላችሁን እየቆጠራችሁ ለጭንቀትና ለብቸኝነት እራሳችሁን አታጋልጡ። እያንዳንዱ ችላ የምትሉት ትንሽ ልማዳችሁ እያደር ዋጋ እንደሚያስከፍላችሁ አትርሱ። ከምስጋና የራቀ ሰው ከታሰበለት በረከቱም እንዲሁ እየራቀ ይሔዳል። ስለሁሉም አመስግኑ፣ እለት እለት በልባዊ ምስጋና ውስጣችሁን አድሱ፣ በረከታችሁን ጨምሩ፣ ደስታችሁንም እራሳችሁ ፍጠሩት።