በዳንሻ፣ በሶሮቃና አካባቢው የፅንፈኛው ቡድን አባላት እጅ ሰጥተዋል።
የፅንፈኛው ቡድን አባላት ከነሙሉ ትጥቃቸው በዳንሻ፣ በሶሮቃና አካባቢው በስምሪት ላይ ለሚገኘው የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ኮር የሠራዊት አባላት እጅ እየሰጡ ነው።
የኮሩ የሠራዊት አባላት በአካባቢው የፀጥታ መዋቅር በማደራጀት እና በመቀናጀት ባደረጉት ህግ የማስከበር ኦፕሬሽን የፅንፈኛው ቡድን ተበታትኖ እጁን እንዲሰጥ አድርጓል ያሉት የኮሩ ምክትል አዛዥ ለውጊያ አገልግሎት ድጋፍ ኮሎኔል መዝገቡ ዘሩ አሁን ላይ በቡድኑ ተፅዕኖ ስር የነበረውን አካባቢ በማፅዳትና አንፃራዊ ሰላም እንዲመዘገብ በማድረግ ህዝቡ የተለመደ ተግባሩን እያከናወነ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
የተሰጠውን የሰላም አማራጭ እድል በመጠቀም በርካቶች በሰላም እጃቸውን እየሰጡ እንደሆነ የገለፁት ኮሎኔል መዝገቡ ይህን ሳይጠቀም ወደ ለመደው ዘረፋ፣ ግድያ፣ ውድመት ድርጊቱ የገባው ፀረ-ህዝብ ቡድን ላይ ሠራዊቱ እርምጃ መውሠዱን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
ህዝቡን በመዝረፍና ሰላም በማሳጣት ለከፋ ችግር መዳረጋቸውን የተናገሩት እጅ የሰጡት የቡድኑ አባላት አሁን በተሰጣቸው የሰላም ምህረት በመጠቀም የበደሉትን ህዝብ ለመካስ ከመንግስት ጎን ተሰልፈው በሰላም ማስከበር እና በልማት ስራዎች ተሰማርተው ለመስራት ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል።
የፅንፈኛው ቡድን አባላት ከነሙሉ ትጥቃቸው በዳንሻ፣ በሶሮቃና አካባቢው በስምሪት ላይ ለሚገኘው የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ኮር የሠራዊት አባላት እጅ እየሰጡ ነው።
የኮሩ የሠራዊት አባላት በአካባቢው የፀጥታ መዋቅር በማደራጀት እና በመቀናጀት ባደረጉት ህግ የማስከበር ኦፕሬሽን የፅንፈኛው ቡድን ተበታትኖ እጁን እንዲሰጥ አድርጓል ያሉት የኮሩ ምክትል አዛዥ ለውጊያ አገልግሎት ድጋፍ ኮሎኔል መዝገቡ ዘሩ አሁን ላይ በቡድኑ ተፅዕኖ ስር የነበረውን አካባቢ በማፅዳትና አንፃራዊ ሰላም እንዲመዘገብ በማድረግ ህዝቡ የተለመደ ተግባሩን እያከናወነ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
የተሰጠውን የሰላም አማራጭ እድል በመጠቀም በርካቶች በሰላም እጃቸውን እየሰጡ እንደሆነ የገለፁት ኮሎኔል መዝገቡ ይህን ሳይጠቀም ወደ ለመደው ዘረፋ፣ ግድያ፣ ውድመት ድርጊቱ የገባው ፀረ-ህዝብ ቡድን ላይ ሠራዊቱ እርምጃ መውሠዱን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
ህዝቡን በመዝረፍና ሰላም በማሳጣት ለከፋ ችግር መዳረጋቸውን የተናገሩት እጅ የሰጡት የቡድኑ አባላት አሁን በተሰጣቸው የሰላም ምህረት በመጠቀም የበደሉትን ህዝብ ለመካስ ከመንግስት ጎን ተሰልፈው በሰላም ማስከበር እና በልማት ስራዎች ተሰማርተው ለመስራት ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል።