ሠውዬውን ለምን እደግፈዋለሁ?
የአብይ ፈተና የጀመረው በመጣ በጥቂት ቀን ውስጥ የድጋፍ ሰልፍ ላይ ቦንብ በመወርወር ነበር። ይህ በሆነ በጥቂት ወራት ውስጥ ደግሞ በተቀናጀ ሁኔታ በሚዲያ ከባድ ስሙን የመበከል ተግባር ይፈፀምበት ጀመር።
በአንድ ቡድን Monopoly ተይዞ የነበረውን የደህንነትና የመከላከያ chain of command እንደገና ለማዋቀር ሲሞክር Power vacuum መፈጠሩን ያዩ ጠላቶች ከገዛ ድርጅቱ ባንዳዎች ጋር በፉጨት ተጠራርተው ከ 120 በላይ መፈናቀሎች በሐገሪቱ ላይ በጭካኔ በመፈፀም ሐገሪቱን በአጭር ግዜ ውስጥ በሐገር ውስጥ መፈናቀል ከአለም አንደኛ አድርገው ኢትዮጵያ እየደማች እነሱ ዳር ቆመው ማላገጥ ጀመሩ። ሠውየው ግን ጥርሱን ነክሶ ጉዞውን ቀጠለ። ህዝብ ከባድ ድንጋጤ ውስጥ ገባ።
ያፈሰሱት ደም ያላረካቸው የጥፋት ኔቶርኮች ሚሊየኖችን ለሚዲያ በመመደብ specifically አብይን ሰይጣናዊ መልክ በመስጠት ከህዝቡ ሊነጥሉት ሠሩ። አነስተኛ መፈንቅለ መንግስት ከመሞከር ጀምሮ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ላይ የግድያ ሙከራ እከማቀነባበር እቅድ ነደፉ። ሠውየውን ግን ማቆም የሚችል እቅድና ሴራ ፈፅሞ ሊፈጠር አልቻለም። ጉዞውን ቀጠለ።
አንዱ የኦሮሞ ጠላት አረገው። ሌላው የአማራ ጠላት ነው ብሎ የፕሮፖጋንዳ ዘመቻ ከፈተበት። የገዛ የሚመራትን ሐገር ህዝብ አፈናቀለ የሚል የሞኝ ዘመቻ ተከፈተበት። እኔ በዚህ ሁሉ ነገር ውስጥ የሚፈጠሩትን ነገሮች ከቅርብ ሆኜ ታዝቢያለሁ። የሰውዬውን ልፋትና በሱ ላይ የተከፈተውን የማያቋርጥ ዘመቻና የጠላትን ክፋትም አይቻለሁ።
ሁሉ እንዳልተሳካ ያዩ ጠላቶች የመጨረሻ አማራጭ ያሉትን ጦርነት ከፈቱ። የጦርነቱ አስከፊ ጎን መከላከያ ሠራዊታችን የተመታው ውስጡ ባሉ ከሃዲዎች መሆኑ ነበር። ባመነው ተከዳ። ከጀርባ ተወጋ። ግዜ ጠብቀው ጦርነት ከፈቱበት። ነገር ግን ይህ ሁሉ እልቂትና የሚዲያ ዘመቻ ያላሸነፈው የኢትዮጵያ ህዝብ ከአብይና ከመከላከያ ጎን ተሰለፈ ሠውየው የአለም አቀፍ ጫናና የዲስኩር ጋጋታ አድርገው ወደአዲስ አበባ ተጠጋን ሲሉ ጭራሽ ወደጦር ሜዳ ሄዶ ፊት ለፊት እንደወንድ ገጠማቸው። ግዙፍ የሚመስለውንና በአውሮፕላን ሳይቀር ከካይሮ መሳሪያ ይላክለት የነበረውን ጎልያድ በፈጣሪ ድጋፍ ድል አደረገ። የሚገርመው ድል ማድረጉ አይደለም። ይህን ሁሉ ያደረገውን አካል ሊያጠፋ ሲችል በድሉ አፋፍ ላይ ቆሞ የይቅርታ እጁን ዘረጋ።
ፈተናው ቀጠለ። የኢትዮጵያ ጠላቶች አልተኙም። የብሔራቸውን ካባ ለብሰው በነፃ አውጪ ስም እዚያም እዚም ተደራጁ። ሐገራቸው ላይ ከግብፅ እስከሶማሊያ ከሐገር ቤት እስከአንታርቲካ የሚዘረጋ የጥፋት ሴራ ይሸርባሉ። ሐገሪቱን እረፍት መንሳትና ሠውየውን የማቆም ዘመቻው ቀጠለ። የኢትዮጵያ ህዝብ አሁንም ይታዘባል።
ሠውየውን ማከብረው በፈተኑት ቁጥር ህልሙ ስለሚጨምር ነው። ጦርነት መሀል አባይን ይገነባል። እሳት መሀል ቆሞ ወደብ ያልማል። የትኛውንም አይነት ፈተና ብትደቅንበት ከመርሀግብሩ ፈቀቅ አታደርገውም። ሊያጠፉት የሚያሴሩትን ሳይቀር አሸንፏቸው ሊያጠፋቸው ሲችል ለይቅርታ እጁን ሲዘረጋ ደጋግሜ አይቸዋለሁ።
ባጭሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በኢትዮጵያ ታሪክ የትኛውም መሪ ያልገጠመውን ፈተና በስድስት አመት ውስጥ ተፈትኖ ያለፈ። እንደወርቅ በእሳት የነጠረና ኢትዮጵያን ከመፍረስ የታደገ መሪ መሆኑን እኔ ሁሉን ነገር ከቅርብ ሆኜ የተመለከትኩት ናትናኤል መኮንን ህያው ምስክር ነኝ።
የአብይ ፈተና የጀመረው በመጣ በጥቂት ቀን ውስጥ የድጋፍ ሰልፍ ላይ ቦንብ በመወርወር ነበር። ይህ በሆነ በጥቂት ወራት ውስጥ ደግሞ በተቀናጀ ሁኔታ በሚዲያ ከባድ ስሙን የመበከል ተግባር ይፈፀምበት ጀመር።
በአንድ ቡድን Monopoly ተይዞ የነበረውን የደህንነትና የመከላከያ chain of command እንደገና ለማዋቀር ሲሞክር Power vacuum መፈጠሩን ያዩ ጠላቶች ከገዛ ድርጅቱ ባንዳዎች ጋር በፉጨት ተጠራርተው ከ 120 በላይ መፈናቀሎች በሐገሪቱ ላይ በጭካኔ በመፈፀም ሐገሪቱን በአጭር ግዜ ውስጥ በሐገር ውስጥ መፈናቀል ከአለም አንደኛ አድርገው ኢትዮጵያ እየደማች እነሱ ዳር ቆመው ማላገጥ ጀመሩ። ሠውየው ግን ጥርሱን ነክሶ ጉዞውን ቀጠለ። ህዝብ ከባድ ድንጋጤ ውስጥ ገባ።
ያፈሰሱት ደም ያላረካቸው የጥፋት ኔቶርኮች ሚሊየኖችን ለሚዲያ በመመደብ specifically አብይን ሰይጣናዊ መልክ በመስጠት ከህዝቡ ሊነጥሉት ሠሩ። አነስተኛ መፈንቅለ መንግስት ከመሞከር ጀምሮ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ላይ የግድያ ሙከራ እከማቀነባበር እቅድ ነደፉ። ሠውየውን ግን ማቆም የሚችል እቅድና ሴራ ፈፅሞ ሊፈጠር አልቻለም። ጉዞውን ቀጠለ።
አንዱ የኦሮሞ ጠላት አረገው። ሌላው የአማራ ጠላት ነው ብሎ የፕሮፖጋንዳ ዘመቻ ከፈተበት። የገዛ የሚመራትን ሐገር ህዝብ አፈናቀለ የሚል የሞኝ ዘመቻ ተከፈተበት። እኔ በዚህ ሁሉ ነገር ውስጥ የሚፈጠሩትን ነገሮች ከቅርብ ሆኜ ታዝቢያለሁ። የሰውዬውን ልፋትና በሱ ላይ የተከፈተውን የማያቋርጥ ዘመቻና የጠላትን ክፋትም አይቻለሁ።
ሁሉ እንዳልተሳካ ያዩ ጠላቶች የመጨረሻ አማራጭ ያሉትን ጦርነት ከፈቱ። የጦርነቱ አስከፊ ጎን መከላከያ ሠራዊታችን የተመታው ውስጡ ባሉ ከሃዲዎች መሆኑ ነበር። ባመነው ተከዳ። ከጀርባ ተወጋ። ግዜ ጠብቀው ጦርነት ከፈቱበት። ነገር ግን ይህ ሁሉ እልቂትና የሚዲያ ዘመቻ ያላሸነፈው የኢትዮጵያ ህዝብ ከአብይና ከመከላከያ ጎን ተሰለፈ ሠውየው የአለም አቀፍ ጫናና የዲስኩር ጋጋታ አድርገው ወደአዲስ አበባ ተጠጋን ሲሉ ጭራሽ ወደጦር ሜዳ ሄዶ ፊት ለፊት እንደወንድ ገጠማቸው። ግዙፍ የሚመስለውንና በአውሮፕላን ሳይቀር ከካይሮ መሳሪያ ይላክለት የነበረውን ጎልያድ በፈጣሪ ድጋፍ ድል አደረገ። የሚገርመው ድል ማድረጉ አይደለም። ይህን ሁሉ ያደረገውን አካል ሊያጠፋ ሲችል በድሉ አፋፍ ላይ ቆሞ የይቅርታ እጁን ዘረጋ።
ፈተናው ቀጠለ። የኢትዮጵያ ጠላቶች አልተኙም። የብሔራቸውን ካባ ለብሰው በነፃ አውጪ ስም እዚያም እዚም ተደራጁ። ሐገራቸው ላይ ከግብፅ እስከሶማሊያ ከሐገር ቤት እስከአንታርቲካ የሚዘረጋ የጥፋት ሴራ ይሸርባሉ። ሐገሪቱን እረፍት መንሳትና ሠውየውን የማቆም ዘመቻው ቀጠለ። የኢትዮጵያ ህዝብ አሁንም ይታዘባል።
ሠውየውን ማከብረው በፈተኑት ቁጥር ህልሙ ስለሚጨምር ነው። ጦርነት መሀል አባይን ይገነባል። እሳት መሀል ቆሞ ወደብ ያልማል። የትኛውንም አይነት ፈተና ብትደቅንበት ከመርሀግብሩ ፈቀቅ አታደርገውም። ሊያጠፉት የሚያሴሩትን ሳይቀር አሸንፏቸው ሊያጠፋቸው ሲችል ለይቅርታ እጁን ሲዘረጋ ደጋግሜ አይቸዋለሁ።
ባጭሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በኢትዮጵያ ታሪክ የትኛውም መሪ ያልገጠመውን ፈተና በስድስት አመት ውስጥ ተፈትኖ ያለፈ። እንደወርቅ በእሳት የነጠረና ኢትዮጵያን ከመፍረስ የታደገ መሪ መሆኑን እኔ ሁሉን ነገር ከቅርብ ሆኜ የተመለከትኩት ናትናኤል መኮንን ህያው ምስክር ነኝ።