#መድኃኔዓለም
፩. ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእርጋታው የተነሣ "የተቀጠቀጠን ሸምበቆ አይሰብርም የሚጤስን የጧፍ ክርም አያጠፋም" ተብሏል (ማቴ.12፥20)። የእርጋታ መምህር ነው።
፪. የትሕትና መምህር ነው።"ከእኔም ተማሩ፥ እኔ የዋህ በልቤም ትሑት ነኝና፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ" እንዲል (ማቴ.11፥29)።
፫. የይቅርታ መምህር ነው። በመስቀል ተሰቅሎ ይቅርታን ለሰው ልጅ ያደለ እርሱ ነው። "ኢየሱስም፦ አባት ሆይ፥ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው አለ" እንዲል (ሉቃ.23፥34)።
፬. የሰላም፣ የፍቅር፣ የትዕግሥት፣ የሰማዕትነት በጠቅላላው የመልካም ሥራዎች ሁሉ መምህር እርሱ ነው። እርሱን ሁልጊዜ ማሰብ ለነፍስ ዕረፍት ነው። እኛም ዋና አብነታችን እርሱ ስለሆነ መልካም ሥራዎችን ሁሉ አባታችንን እርሱን መስለን እንሥራ።
✝እንኳን አደረሳችሁ አደረሰን👏
፩. ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእርጋታው የተነሣ "የተቀጠቀጠን ሸምበቆ አይሰብርም የሚጤስን የጧፍ ክርም አያጠፋም" ተብሏል (ማቴ.12፥20)። የእርጋታ መምህር ነው።
፪. የትሕትና መምህር ነው።"ከእኔም ተማሩ፥ እኔ የዋህ በልቤም ትሑት ነኝና፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ" እንዲል (ማቴ.11፥29)።
፫. የይቅርታ መምህር ነው። በመስቀል ተሰቅሎ ይቅርታን ለሰው ልጅ ያደለ እርሱ ነው። "ኢየሱስም፦ አባት ሆይ፥ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው አለ" እንዲል (ሉቃ.23፥34)።
፬. የሰላም፣ የፍቅር፣ የትዕግሥት፣ የሰማዕትነት በጠቅላላው የመልካም ሥራዎች ሁሉ መምህር እርሱ ነው። እርሱን ሁልጊዜ ማሰብ ለነፍስ ዕረፍት ነው። እኛም ዋና አብነታችን እርሱ ስለሆነ መልካም ሥራዎችን ሁሉ አባታችንን እርሱን መስለን እንሥራ።
✝እንኳን አደረሳችሁ አደረሰን👏