የብርሃን እናቱ ሆይ ካንቺ በነሳው ስጋ እኛነታችንን አከበረ፡፡መዐዛሽ ስቦት አንችን በወደደ ጊዜ ድህነታችን ተሰራ፡፡ድንግል ሆይ እውነተኛው የህይወት እንጀራ : ጣፋጩን የነፍስ መጠጥ አማናዊው የፅድቅ ብርሀን የፈነጠቀብሽ ነሽና ከትውልድ መሀል ብፅዕናሽን እንናገራለን፡፡ጥማችንን የቆረጠ ጥዑም ወይን፡ረሀባችንን ያጠፋ እውነተኛው መብል ካንቺ ወጥቶልናልና እንወድሻለን፡፡ምስራቃዊት በራችን ሆይ ከሴቶች አንችን የሚመስል የለም፡፡ባንቺ ላይ ስለተደረገልን ታላቅ ነገር ዛሬም ለዘላለምም ስምሽን እናገናለን፡፡
ዝምተኛይቱ ድንግል ሆይ አንቺ አንገታቸውን እንደሚያገዝፉ የአይሁድ ሴቶች አይደለሽም።በትሕትና ተልመሽ በንፅሕና አጊጠሽ የባህርያችንን መመኪያ ያስገኘሽልን የፅድቅ በራችን ነሽ። አንችን ማመስገን የነፍስ ምግብ የህሊና እርካታ ነው።ስናመሰግንሽ እናርፋለን ስናርፍ እናመሰግንሻለን።ክብርሽ ከሰማይ ምስጋናሽም ከአርያም ነውና አንችን ለማመስገን ልቦናችን ይብራ አሜን።🌷
ዝምተኛይቱ ድንግል ሆይ አንቺ አንገታቸውን እንደሚያገዝፉ የአይሁድ ሴቶች አይደለሽም።በትሕትና ተልመሽ በንፅሕና አጊጠሽ የባህርያችንን መመኪያ ያስገኘሽልን የፅድቅ በራችን ነሽ። አንችን ማመስገን የነፍስ ምግብ የህሊና እርካታ ነው።ስናመሰግንሽ እናርፋለን ስናርፍ እናመሰግንሻለን።ክብርሽ ከሰማይ ምስጋናሽም ከአርያም ነውና አንችን ለማመስገን ልቦናችን ይብራ አሜን።🌷