የፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ̔ፕሬዝዳንሻል ሜንተርሽፕ̔ ሰልጣኞች በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ተመረቁ፡፡
የሜንተርሽፕ ፕሮግራሙ በአምስት ዩኒቨርሲቲዎች ማለትም በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ፣ በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፣ በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ፣ በደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ እና በደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ለሚገኙ ሴት ተማሪዎች የተለያዩ ክህሎቶች ማሳደጊያ የማማከር ስልጠናዎችን ሲሰጥ ቆይቷል፡፡
ከአምስቱ ዩኒቨርሲቲዎች በተለያየ ዙር ስልጠናውን ሲከታተሉ የነበሩ ተማሪዎች የምርቃት እና የፕሮጀክቱ ማጠቃለያ መርሐግብር ተካሄዷል፡፡
በአጠቃላይ በአምስቱ ዩኒቨርሲቲዎች ቁጥራቸው 500 የሚሆኑ የፕሬዝዳንሻል ሜንተርሺፕ ስልጠና (Presidential Mentorship Program) ሲከታተሉ የቆዩ ተማሪዎች ተመርቀዋል፡፡
ፕሮግራሙ በ Institute of International Education አማካኝነት በአመራር ብቁ የሆኑ ሴቶችን ለማፍራት ከአራት ዓመት በፊት የተጀመረ መርሐግብር ነው፡፡ #AASTU
@tikvahuniveristy
የሜንተርሽፕ ፕሮግራሙ በአምስት ዩኒቨርሲቲዎች ማለትም በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ፣ በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፣ በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ፣ በደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ እና በደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ለሚገኙ ሴት ተማሪዎች የተለያዩ ክህሎቶች ማሳደጊያ የማማከር ስልጠናዎችን ሲሰጥ ቆይቷል፡፡
ከአምስቱ ዩኒቨርሲቲዎች በተለያየ ዙር ስልጠናውን ሲከታተሉ የነበሩ ተማሪዎች የምርቃት እና የፕሮጀክቱ ማጠቃለያ መርሐግብር ተካሄዷል፡፡
በአጠቃላይ በአምስቱ ዩኒቨርሲቲዎች ቁጥራቸው 500 የሚሆኑ የፕሬዝዳንሻል ሜንተርሺፕ ስልጠና (Presidential Mentorship Program) ሲከታተሉ የቆዩ ተማሪዎች ተመርቀዋል፡፡
ፕሮግራሙ በ Institute of International Education አማካኝነት በአመራር ብቁ የሆኑ ሴቶችን ለማፍራት ከአራት ዓመት በፊት የተጀመረ መርሐግብር ነው፡፡ #AASTU
@tikvahuniveristy