ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ "የተማሪዎቹን ደህንነት" በተመለከተ በተለያዩ የማኅበራዊ ትስስር ገፆች እየተናፈሰ ያለው መረጃ ሐሰት መሆኑን ገለፀ፡፡
ሐሰተኛ መረጃዎቹ "የፆታዊ ጥቃት መከሰታቸውን እንዲሁም የተማሪዎች ህይወት ማለፉን" የሚገልጹ ሲሆን፤ አሉባልታዎቹ ሙሉ በሙሉ ሐሰት መሆናቸውን ዩኒቨርሲቲው ባወጣው መግለጫ አሳውቋል፡፡
"የተማሪዎቻችንን ደህንነት ማስጠበቅ የቅድሚያ ቅድሚያ የምንሰጠው ጉዳይ ነው" ያለው ዩኒቨርሲቲው፤ በተቋሙ ውስጥ ምንም አይነት ፆታዊ ጥቃት፣ ጉዳት እና ሞት አልተፈጠረም ብሏል፡፡
ዩኒቨርሲቲው የአሉባልታዎቹን ምንጭ አጣርቶ ተገቢውን እርምጃ እንደሚወስድ አሳውቋል፡፡ ሐሰተኛ መረጃዎቹን ያሰራጩ የማኅበራዊ ትስስር ገፆች የትኞቹ እንደሆኑ ዩኒቨርሲቲው አልገለፀም፡፡
@tikvahuniveristy
ሐሰተኛ መረጃዎቹ "የፆታዊ ጥቃት መከሰታቸውን እንዲሁም የተማሪዎች ህይወት ማለፉን" የሚገልጹ ሲሆን፤ አሉባልታዎቹ ሙሉ በሙሉ ሐሰት መሆናቸውን ዩኒቨርሲቲው ባወጣው መግለጫ አሳውቋል፡፡
"የተማሪዎቻችንን ደህንነት ማስጠበቅ የቅድሚያ ቅድሚያ የምንሰጠው ጉዳይ ነው" ያለው ዩኒቨርሲቲው፤ በተቋሙ ውስጥ ምንም አይነት ፆታዊ ጥቃት፣ ጉዳት እና ሞት አልተፈጠረም ብሏል፡፡
ዩኒቨርሲቲው የአሉባልታዎቹን ምንጭ አጣርቶ ተገቢውን እርምጃ እንደሚወስድ አሳውቋል፡፡ ሐሰተኛ መረጃዎቹን ያሰራጩ የማኅበራዊ ትስስር ገፆች የትኞቹ እንደሆኑ ዩኒቨርሲቲው አልገለፀም፡፡
@tikvahuniveristy