(ዘ-ሐበሻ ዜና) የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፖሊስ ትናንት በፃፈው ደብዳቤ ህወሀት ያካሄደውን ህዝባዊ ኮንፈረንስ ተከትሎ በኮንፈረንሱ የተላለፉ ውሳኔዎችን ለመደገፍ በሚል ዛሬ ጥር 18 ሰላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ ጥያቄ እንደቀረበለትና ባለው ሁኔታ "የፀጥታ ሽፋን መስጠት ስለማይቻል ሰልፉን ለሌላ ጊዜ እንዲያስተላለፉት ማሳሰቢያ" ቢሰጥም፣ ሰላማዊ ሰልፉ ግን በትግራይ የተለያዩ ከተሞች ዛሬ እየተካሄዱ መሆናቸውን ከስፍራው የወጡ መረጃዎች አመልክተዋል።
ሰልፎቹ እየተካሄዱባቸው ካሉባቸው ከተሞች መካከል መቀሌና ሽሬ የሚጠቀሱ ሲሆን፣ ሰልፈኞችም የተለያዩ ጥያቄዎችን አንስተዋል።
ከነዚህም መካከል "የፕሪቶሪያ ስምምነት መፈፀም ለትግራይ እና ለአፍሪካ ቀንድ ህዝቦች የሰላም ዋስትና ነው!"፣ "ህወሀት ያካሄደውን ህዝባዊ ኮንፈረንስ፣ ድርጅታችን ህወሓት እና የትግራይ ሰራዊት ያሳለፏቸው ውሳኔዎች በአስቸኳይ ተግባራዊ መሆን አለባቸው!!"፣ "የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር በአስቸኳይ ሊስተካከል ይገባል!!"፣ "የፕሪቶሪያው ስምምነት አሁኑኑ ተግባራዊ ይደረግ"፣ " የተፈናቀሉ እና የተፈናቀሉ ወገኖቻችን በአስቸኳይ ወደ ቤታቸው ይመለሱ!!"፣ "የፓርቲያችን ሕጋዊ እውቅና በአስቸኳይ ይመለስ!!"፣ "ሰራዊታችንን የማፍረስ ሴራ አንቀበልም!!"፣ "የውጭ ጣልቃ ገብነቶችን እንቃወማለን" የሚሉና ሌሎችም መፈክሮች እየተሰሙ ነው።
ሰልፎቹ እየተካሄዱባቸው ካሉባቸው ከተሞች መካከል መቀሌና ሽሬ የሚጠቀሱ ሲሆን፣ ሰልፈኞችም የተለያዩ ጥያቄዎችን አንስተዋል።
ከነዚህም መካከል "የፕሪቶሪያ ስምምነት መፈፀም ለትግራይ እና ለአፍሪካ ቀንድ ህዝቦች የሰላም ዋስትና ነው!"፣ "ህወሀት ያካሄደውን ህዝባዊ ኮንፈረንስ፣ ድርጅታችን ህወሓት እና የትግራይ ሰራዊት ያሳለፏቸው ውሳኔዎች በአስቸኳይ ተግባራዊ መሆን አለባቸው!!"፣ "የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር በአስቸኳይ ሊስተካከል ይገባል!!"፣ "የፕሪቶሪያው ስምምነት አሁኑኑ ተግባራዊ ይደረግ"፣ " የተፈናቀሉ እና የተፈናቀሉ ወገኖቻችን በአስቸኳይ ወደ ቤታቸው ይመለሱ!!"፣ "የፓርቲያችን ሕጋዊ እውቅና በአስቸኳይ ይመለስ!!"፣ "ሰራዊታችንን የማፍረስ ሴራ አንቀበልም!!"፣ "የውጭ ጣልቃ ገብነቶችን እንቃወማለን" የሚሉና ሌሎችም መፈክሮች እየተሰሙ ነው።