✔️መልስ፦ በርስቶች መካከል ብታድሩ ማለት የከነዓን ሰዎች ወደ ወረሷት ወደሴም ዕፃ ብትደርሱ እንደ ርግብ ክንፎች በቅጠልያ ወርቅም እንደተለበጡ ላባዎቿ ትሆናላችሁ። ይህም ማለት ወርቅ ጽሩይ እንደሆነ ልብን የምታጠራ ሕግን ታገኛላችሁ ማለት ነው።
▶️፲፭. መዝ.67፥17 ላይ የእግዚአብሔር ሠረገላዎች የተባሉ እነማን ናቸው?
✔️መልስ፦ የእግዚአብሔር ሠረገላዎች የሚባሉት በእግዚአብሔር ሕግ የሚመሩ እስራኤላውያን ናቸው።
▶️፲፮. መዝ.67፥18 "ምርኮን ማርከኽ ወደ ሰማይ ወጣኽ። ስጦታኽንም ለሰዎች ሰጠኽ። ያድሩ ዘንድ ይክዱ ነበርና'' የሚለውን ቢያብራሩልኝ።
✔️መልስ፦ ምርኮን ማርከህ ወደ ሰማይ ወጣህ ማለት ለጊዜው እስራኤላውያንን ከባቢሎን ምርኮኝነት አውጥተህ በዘሩባቤል አማካኝነት ወደ ኢየሩሳሌም መለስካቸው ማለት ነው። በሌላ አገላለጽ (ኦ ክርስቶስ) ነፍሳትን ከሲኦል አውጥተህ ወደ ገነት አገባሀቸው ማለት ነው። ስጦታህንም ለሰዎች ሰጠህ ማለት ሚጠተ ሥጋን ለእስራኤል ሰጠህ፣ ሚጠተ ነፍስን ደግሞ ለነፍሳት ሰጠህ ማለት ነው። ሚጠትን ባትሰጥ ኖሮ ይክዱ ነበር ማለት ከመከራው ጽናት የተነሣ ከአምልኮተ እግዚአብሔር ይወጡ ነበር ማለት ነው።
▶️፲፯. መዝ.67፥20 ላይ "የሞት መንገድ የእግዚአብሔር ነው'' ሲል ምን ለማለት ነው?
✔️መልስ፦ የሞት መንገድ የእግዚአብሔር ነው ማለት የሰውን ነፍሱን ከሥጋው የመለየት ሥልጣን የእግዚአብሔር ነው ማለት ነው።
▶️፲፰. መዝ.67፥21 ላይ ''በጠጉራቸው ጫፍም በደላቸው ይኼዳል'' ሲል ምን ማለቱ ነው?
✔️መልስ፦ ይህ ማለት ማዕበል ሞገዱ በራሳቸው ላይ ይሔዳል ማለት ነው። ይኸውም ለበደሉ እስራኤላውያን ታላቅ መከራ ይመጣባቸዋል ማለት ነው። በሌላ አገላለጽ የምእመናን ኃጢአታቸው በክርስቶስ ይቅር ይባላል ማለት ነው።
▶️፲፱. መዝ.67፥22 ላይ ''ወጥቼ እመለሳለኹ'' ይላል። ቢብራራ።
✔️መልስ፦ ይህ ስለክርስቶስም ያስተረጉማል። (ይቤ ክርስቶስ) ወደ ሰማይ ዐርጌ እመለሳለሁ ይላል። ይህም ማለት በምጽአት መጥቶ ፍርድ እንደሚሰጥ ያመለክታል።
▶️፳. መዝ.67፥23 ላይ ''እግሮችኽ በደም ይነከሩ ዘንድ የውሻዎችኽ ምላስ በጠላቶች ላይ ነው'' ማለቱ ምንድን ነው?
✔️መልስ፦ እግሮችህ በደም ይነከሩ ዘንድ የተባለ ክርስቶስ በመስቀል እግሮቹ ተቸንክረው በደም እንደሚነከሩ ያመለክታል። ሰላም ለአጽፋረ እግርከ በደመ ቅንዋት እለ ተጠምዓ እንዳለ ደራሲ። የውሾችህ ምላስ በጠላቶች ላይ ነው ማለት ውሻ ለጌታው ታማኝ እንደሆነ በአንተ የሚያምኑ ምእመናን አንደበት በአጋንንት ላይ ነው ማለት ነው።
▶️፳፩. "ቀንድና ጥፍር ካበቀለ ከእንቦሳ ይልቅ እግዚአብሔርን ደስ ያሠኘዋል" ይላል (መዝ.68፥31)። ምን ማለት እንደሆነ ቢያብራሩልን?
✔️መልስ፦ ቀንድና ጥፍር ያበቀለ እንቦሳ የተባለው ለቤተ መቅደስ የሚሠዋውን መሥዋዕት ነው። ከዚህ መሥዋዕት ይልቅ እግዚአብሔርን ደስ ያሰኘዋል የተባለ ግን ከፍ ብሎ እንደተገለጠው ምስጋና መሆኑን ያመለክታል።
▶️፳፪. ''በምሥራቅ በኩል ወደ ሰማየ ሰማያት ለወጣ ለእግዚአብሔር ዘምሩ" ሲል ምን ማለት ነው? ቢብራራልኝ (መዝ.67፥33)።
✔️መልስ፦ በምሥራቅ በኩል ወደ ሰማየ ሰማያት ለወጣ ለእግዚአብሔር ዘምሩ ማለት ትሩፋንን ይዞ ከፋርስ ባቢሎን ወደ ኢየሩሳሌም ለወጣ ለእግዚአብሔር ምስጋና አቅርቡ ማለት ነው። በሌላ አገላለጽ ነፍሳትን ከሲኦል ወደ ገነት ለመለሰ ለእግዚአብሔር ምስጋና አቅርቡ ማለት ነው።
▶️፳፫. መዝ.68፥6 ''የእስራኤል አምላክ ሆይ የሚሹኽ በእኔ አይነወሩ'' ሲል ምን ማለት ነው?
✔️መልስ፦ ይህ ማለት እግዚአብሔር ሆይ አንተን በሕግ በአምልኮ የሚሹህ ነቢያት ካህናት የእኔ መከራ አይድረስባቸው ይላል ዳዊት።
▶️፳፬. መዝ.70፥6 ''በማሕፀን ውስጥም አንተ ሸሸግኸኝ'' ሲል ምን ማለት ነው?
✔️መልስ፦ በማሕፀን ውስጥ ሸሸግኸኝ ማለት በጽንስነቴ እንዳልሞት አንተ ጠበቅኸኝ ማለት ነው።
▶️፳፭. መዝ.70፥7 ''እንደ ጥንግ ኾንኹ" ሲል ጥንግ ምንድን ነው?
✔️መልስ፦ ጥንግ የሚባለው እንደ ኳስ ክብ የሆነች በጣም ትንሽ ነገር ስትሆን በገና ጨዋታ ተጫዋቾች የሚጫወቱባት የሚለጓት ነገር ናት።
▶️፳፮. መዝ.62፥8 ላይ "ነፍሴ በዃላኽ ተከታተለች እኔንም ቀኝኽ ተቀበለችኝ" ይላል። ቢብራራልኝ።
✔️መልስ፦ ነፍሴ በኋላህ ተከታተለች ማለት በአምልኮ አንተን ተከተለች ማለት ነው። ስለዚህም ቀኝህ ተቀበለችኝ ማለት ረድኤትህን ሰጠኸኝ ማለት ነው።
▶️፳፯. መዝ.64፥2 "ሥጋ ዅሉ ጸሎትን ወደምትሰማ ወደ አንተ ይመጣል" ይላል። ሥጋ ሲል ምን ማለት ነው?
✔️መልስ፦ ሥጋ ብሎ የጠቀሰው ሰውን ነው። ሰውን አንዳንድ ጊዜ ሥጋ አንዳንድ ጊዜ ነፍስ ብሎ ይጠራዋልና ነው። ስለዚህ ሰው ሁሉ፣ ሥጋዊ ደማዊ ፍጥረት ሁሉ ወደ አንተ ይመጣል ማለት ጸሎቱን ያቀርባል ማለት ነው።
▶️፳፰. መዝ.65፥18 "በልቤስ በደልን አይቼ ብኾን ጌታ አይሰማኝም ነበር" ይላል። ይህ ምን ማለት ነው?
✔️መልስ፦ ዳዊት ይህንን የተናገረው ስለትሩፋን ነው። ከትሩፋንም ስለአስቴርና ስለመርዶክዮስ ነው። መርዶክዮስ በልቡናዬ ቂም በቀል፣ በቃሌ መበደል፣ በእጄ መግደል ቢኖር እግዚአብሔር ልመናዬን ባልሰማኝም ነበር ይላል።
▶️፳፱. "እስከ መቼ በሰው ላይ ትቆማላችሁ? እናንተ ሁላችሁ እንዳዘነበለ ግድግዳ እንደ ፈረሰም ቅጥር ትገድላላችሁ" ይላል (መዝ.61፥3)። እንዳዘነበለ ግድግዳ እንደ ፈረሰም ቅጥር ትገድላላችሁ ሲል ምን ማለት ነው?
✔️መልስ፦ ያዘነበለን ግድግዳና የፈረሰን አጥር ሌላ ሰው እንዳይጎዳ እንደምታፈርሱት ሁሉ መቃብያንን ለምን ትገድሏቸዋላችሁ ብሎ ዳዊት ይናገራል። ደግ ሆነው ሳለ መግደል አይገባችሁም ነበር ማለቱ ነው።
▶️፴. "ነገር ግን የሰው ልጆች ከንቱ ናቸው። የሰው ልጆችም ሐሰተኞች ናቸው። በሚዛንም ይበድላሉ። እነርሱስ በፍጹም ከንቱ ናቸው" ይላል (መዝ.61፥9)። በሚዛንም ይበድላሉ ሲል ምን ማለት ነው?
✔️መልስ፦ በሚዛን ይበድላሉ ማለት በሚዛን ያታልላሉ ማለት ነው። ይኸውም በታናሽ ሚዛን ሰጥተው በታላቅ ሚዛን ይቀበላሉ ወይም በታላቅ ተቀብለው በታናሽ ይሰጣሉ ማለት ነው። ምሥጢሩ ሕግን ያሳብላሉ ማለት ያፈርሳሉ ማለት ነው።
▶️፴፩. "የባሕሩን ጥልቀት የሞገድንም ጩኸት ታናውጣለህ" ይላል (መዝ.64፥7)። ምን ማለት ነው?
✔️መልስ፦ የባሕርን ጥልቀት የሞገድንም ጩኸት ታናውጣለህ ማለት በጥልቅ ባሕር ሞገድ ፈርዖንን አሰጠምክ ማለት ነው።
▶️፴፪. "ትልሟን ታረካለህ። ቦይዋንም ታስተካክላለህ። በነጠብጣብ ታለሰልሳታለህ። ቡቃያዋንም ትባርካለህ። በቸርነትህ ዓመትን ታቀዳጃለህ። ምድረ በዳውም ስብን ይጠግባል። የምድረ በዳ ተራሮች ይረካሉ። ኮረብቶችም በደስታ ይታጠቃሉ። ማሰማርያዎች መንጎችን ለበሱ። ሸለቆችም በእህል ተሸፈኑ። በደስታ ይጮኻሉ ይዘምራሉም" ይላል (መዝ.65፥10-12)። የዚህ ትርጓሜው ምንድን ነው?
✔️መልስ፦ ከላይ ያለው ስለዚህች ዓለም የተነገረ ነው። እግዚአብሔር ትልሟን በዝናም አርክቶ፣ ወንዞቿን አስተካክሎ ምድር ቡቃያን እንደምታወጣ ያመለክታል። በቸርነትህ ዓመትን ታቀዳጃለህ ማለት በቸርነትህ ዘመን የተገኘውን ዓመት ትባርካለህ በዘመኑ የሚገኘውን እህሉንም ታበዛለህ ማለት ነው። ተራሮች ይረካሉ፣ ኮረብቶች በደስታ ይታጠቃሉ ማለት አብበው ለምልመው ያሸበርቃሉ ማለት ነው። ማሰማሪያዎች መንጎችን ለበሱ ማለት አውራ በጎች ሴት በጎችን ይንጠላጠሏቸዋል ማለት ነው። ሸለቆዎች በእህል ተሸፈኑ፣ በደስታ ይጮኻሉ ይዘምራሉ
▶️፲፭. መዝ.67፥17 ላይ የእግዚአብሔር ሠረገላዎች የተባሉ እነማን ናቸው?
✔️መልስ፦ የእግዚአብሔር ሠረገላዎች የሚባሉት በእግዚአብሔር ሕግ የሚመሩ እስራኤላውያን ናቸው።
▶️፲፮. መዝ.67፥18 "ምርኮን ማርከኽ ወደ ሰማይ ወጣኽ። ስጦታኽንም ለሰዎች ሰጠኽ። ያድሩ ዘንድ ይክዱ ነበርና'' የሚለውን ቢያብራሩልኝ።
✔️መልስ፦ ምርኮን ማርከህ ወደ ሰማይ ወጣህ ማለት ለጊዜው እስራኤላውያንን ከባቢሎን ምርኮኝነት አውጥተህ በዘሩባቤል አማካኝነት ወደ ኢየሩሳሌም መለስካቸው ማለት ነው። በሌላ አገላለጽ (ኦ ክርስቶስ) ነፍሳትን ከሲኦል አውጥተህ ወደ ገነት አገባሀቸው ማለት ነው። ስጦታህንም ለሰዎች ሰጠህ ማለት ሚጠተ ሥጋን ለእስራኤል ሰጠህ፣ ሚጠተ ነፍስን ደግሞ ለነፍሳት ሰጠህ ማለት ነው። ሚጠትን ባትሰጥ ኖሮ ይክዱ ነበር ማለት ከመከራው ጽናት የተነሣ ከአምልኮተ እግዚአብሔር ይወጡ ነበር ማለት ነው።
▶️፲፯. መዝ.67፥20 ላይ "የሞት መንገድ የእግዚአብሔር ነው'' ሲል ምን ለማለት ነው?
✔️መልስ፦ የሞት መንገድ የእግዚአብሔር ነው ማለት የሰውን ነፍሱን ከሥጋው የመለየት ሥልጣን የእግዚአብሔር ነው ማለት ነው።
▶️፲፰. መዝ.67፥21 ላይ ''በጠጉራቸው ጫፍም በደላቸው ይኼዳል'' ሲል ምን ማለቱ ነው?
✔️መልስ፦ ይህ ማለት ማዕበል ሞገዱ በራሳቸው ላይ ይሔዳል ማለት ነው። ይኸውም ለበደሉ እስራኤላውያን ታላቅ መከራ ይመጣባቸዋል ማለት ነው። በሌላ አገላለጽ የምእመናን ኃጢአታቸው በክርስቶስ ይቅር ይባላል ማለት ነው።
▶️፲፱. መዝ.67፥22 ላይ ''ወጥቼ እመለሳለኹ'' ይላል። ቢብራራ።
✔️መልስ፦ ይህ ስለክርስቶስም ያስተረጉማል። (ይቤ ክርስቶስ) ወደ ሰማይ ዐርጌ እመለሳለሁ ይላል። ይህም ማለት በምጽአት መጥቶ ፍርድ እንደሚሰጥ ያመለክታል።
▶️፳. መዝ.67፥23 ላይ ''እግሮችኽ በደም ይነከሩ ዘንድ የውሻዎችኽ ምላስ በጠላቶች ላይ ነው'' ማለቱ ምንድን ነው?
✔️መልስ፦ እግሮችህ በደም ይነከሩ ዘንድ የተባለ ክርስቶስ በመስቀል እግሮቹ ተቸንክረው በደም እንደሚነከሩ ያመለክታል። ሰላም ለአጽፋረ እግርከ በደመ ቅንዋት እለ ተጠምዓ እንዳለ ደራሲ። የውሾችህ ምላስ በጠላቶች ላይ ነው ማለት ውሻ ለጌታው ታማኝ እንደሆነ በአንተ የሚያምኑ ምእመናን አንደበት በአጋንንት ላይ ነው ማለት ነው።
▶️፳፩. "ቀንድና ጥፍር ካበቀለ ከእንቦሳ ይልቅ እግዚአብሔርን ደስ ያሠኘዋል" ይላል (መዝ.68፥31)። ምን ማለት እንደሆነ ቢያብራሩልን?
✔️መልስ፦ ቀንድና ጥፍር ያበቀለ እንቦሳ የተባለው ለቤተ መቅደስ የሚሠዋውን መሥዋዕት ነው። ከዚህ መሥዋዕት ይልቅ እግዚአብሔርን ደስ ያሰኘዋል የተባለ ግን ከፍ ብሎ እንደተገለጠው ምስጋና መሆኑን ያመለክታል።
▶️፳፪. ''በምሥራቅ በኩል ወደ ሰማየ ሰማያት ለወጣ ለእግዚአብሔር ዘምሩ" ሲል ምን ማለት ነው? ቢብራራልኝ (መዝ.67፥33)።
✔️መልስ፦ በምሥራቅ በኩል ወደ ሰማየ ሰማያት ለወጣ ለእግዚአብሔር ዘምሩ ማለት ትሩፋንን ይዞ ከፋርስ ባቢሎን ወደ ኢየሩሳሌም ለወጣ ለእግዚአብሔር ምስጋና አቅርቡ ማለት ነው። በሌላ አገላለጽ ነፍሳትን ከሲኦል ወደ ገነት ለመለሰ ለእግዚአብሔር ምስጋና አቅርቡ ማለት ነው።
▶️፳፫. መዝ.68፥6 ''የእስራኤል አምላክ ሆይ የሚሹኽ በእኔ አይነወሩ'' ሲል ምን ማለት ነው?
✔️መልስ፦ ይህ ማለት እግዚአብሔር ሆይ አንተን በሕግ በአምልኮ የሚሹህ ነቢያት ካህናት የእኔ መከራ አይድረስባቸው ይላል ዳዊት።
▶️፳፬. መዝ.70፥6 ''በማሕፀን ውስጥም አንተ ሸሸግኸኝ'' ሲል ምን ማለት ነው?
✔️መልስ፦ በማሕፀን ውስጥ ሸሸግኸኝ ማለት በጽንስነቴ እንዳልሞት አንተ ጠበቅኸኝ ማለት ነው።
▶️፳፭. መዝ.70፥7 ''እንደ ጥንግ ኾንኹ" ሲል ጥንግ ምንድን ነው?
✔️መልስ፦ ጥንግ የሚባለው እንደ ኳስ ክብ የሆነች በጣም ትንሽ ነገር ስትሆን በገና ጨዋታ ተጫዋቾች የሚጫወቱባት የሚለጓት ነገር ናት።
▶️፳፮. መዝ.62፥8 ላይ "ነፍሴ በዃላኽ ተከታተለች እኔንም ቀኝኽ ተቀበለችኝ" ይላል። ቢብራራልኝ።
✔️መልስ፦ ነፍሴ በኋላህ ተከታተለች ማለት በአምልኮ አንተን ተከተለች ማለት ነው። ስለዚህም ቀኝህ ተቀበለችኝ ማለት ረድኤትህን ሰጠኸኝ ማለት ነው።
▶️፳፯. መዝ.64፥2 "ሥጋ ዅሉ ጸሎትን ወደምትሰማ ወደ አንተ ይመጣል" ይላል። ሥጋ ሲል ምን ማለት ነው?
✔️መልስ፦ ሥጋ ብሎ የጠቀሰው ሰውን ነው። ሰውን አንዳንድ ጊዜ ሥጋ አንዳንድ ጊዜ ነፍስ ብሎ ይጠራዋልና ነው። ስለዚህ ሰው ሁሉ፣ ሥጋዊ ደማዊ ፍጥረት ሁሉ ወደ አንተ ይመጣል ማለት ጸሎቱን ያቀርባል ማለት ነው።
▶️፳፰. መዝ.65፥18 "በልቤስ በደልን አይቼ ብኾን ጌታ አይሰማኝም ነበር" ይላል። ይህ ምን ማለት ነው?
✔️መልስ፦ ዳዊት ይህንን የተናገረው ስለትሩፋን ነው። ከትሩፋንም ስለአስቴርና ስለመርዶክዮስ ነው። መርዶክዮስ በልቡናዬ ቂም በቀል፣ በቃሌ መበደል፣ በእጄ መግደል ቢኖር እግዚአብሔር ልመናዬን ባልሰማኝም ነበር ይላል።
▶️፳፱. "እስከ መቼ በሰው ላይ ትቆማላችሁ? እናንተ ሁላችሁ እንዳዘነበለ ግድግዳ እንደ ፈረሰም ቅጥር ትገድላላችሁ" ይላል (መዝ.61፥3)። እንዳዘነበለ ግድግዳ እንደ ፈረሰም ቅጥር ትገድላላችሁ ሲል ምን ማለት ነው?
✔️መልስ፦ ያዘነበለን ግድግዳና የፈረሰን አጥር ሌላ ሰው እንዳይጎዳ እንደምታፈርሱት ሁሉ መቃብያንን ለምን ትገድሏቸዋላችሁ ብሎ ዳዊት ይናገራል። ደግ ሆነው ሳለ መግደል አይገባችሁም ነበር ማለቱ ነው።
▶️፴. "ነገር ግን የሰው ልጆች ከንቱ ናቸው። የሰው ልጆችም ሐሰተኞች ናቸው። በሚዛንም ይበድላሉ። እነርሱስ በፍጹም ከንቱ ናቸው" ይላል (መዝ.61፥9)። በሚዛንም ይበድላሉ ሲል ምን ማለት ነው?
✔️መልስ፦ በሚዛን ይበድላሉ ማለት በሚዛን ያታልላሉ ማለት ነው። ይኸውም በታናሽ ሚዛን ሰጥተው በታላቅ ሚዛን ይቀበላሉ ወይም በታላቅ ተቀብለው በታናሽ ይሰጣሉ ማለት ነው። ምሥጢሩ ሕግን ያሳብላሉ ማለት ያፈርሳሉ ማለት ነው።
▶️፴፩. "የባሕሩን ጥልቀት የሞገድንም ጩኸት ታናውጣለህ" ይላል (መዝ.64፥7)። ምን ማለት ነው?
✔️መልስ፦ የባሕርን ጥልቀት የሞገድንም ጩኸት ታናውጣለህ ማለት በጥልቅ ባሕር ሞገድ ፈርዖንን አሰጠምክ ማለት ነው።
▶️፴፪. "ትልሟን ታረካለህ። ቦይዋንም ታስተካክላለህ። በነጠብጣብ ታለሰልሳታለህ። ቡቃያዋንም ትባርካለህ። በቸርነትህ ዓመትን ታቀዳጃለህ። ምድረ በዳውም ስብን ይጠግባል። የምድረ በዳ ተራሮች ይረካሉ። ኮረብቶችም በደስታ ይታጠቃሉ። ማሰማርያዎች መንጎችን ለበሱ። ሸለቆችም በእህል ተሸፈኑ። በደስታ ይጮኻሉ ይዘምራሉም" ይላል (መዝ.65፥10-12)። የዚህ ትርጓሜው ምንድን ነው?
✔️መልስ፦ ከላይ ያለው ስለዚህች ዓለም የተነገረ ነው። እግዚአብሔር ትልሟን በዝናም አርክቶ፣ ወንዞቿን አስተካክሎ ምድር ቡቃያን እንደምታወጣ ያመለክታል። በቸርነትህ ዓመትን ታቀዳጃለህ ማለት በቸርነትህ ዘመን የተገኘውን ዓመት ትባርካለህ በዘመኑ የሚገኘውን እህሉንም ታበዛለህ ማለት ነው። ተራሮች ይረካሉ፣ ኮረብቶች በደስታ ይታጠቃሉ ማለት አብበው ለምልመው ያሸበርቃሉ ማለት ነው። ማሰማሪያዎች መንጎችን ለበሱ ማለት አውራ በጎች ሴት በጎችን ይንጠላጠሏቸዋል ማለት ነው። ሸለቆዎች በእህል ተሸፈኑ፣ በደስታ ይጮኻሉ ይዘምራሉ