በአፍዴራና ዳሎል አካባቢ ላሉ የጨውና ፖታሽ አምራች ኢንዱስትሪዎች ኤሌክትሪክ ለማቅረብ እየተሰራ ነው
በአፋር ክልል ለሚገኙ የጨውና ፖታሽ አምራች ኢንዱስትሪዎች እንዲሁም 38 የገጠር ከተሞችና መንደሮች የ24 ሰአት የኤሌክትሪክ አገልግሎት ለማቅረብ እየተሰራ ነው፡፡
ለፕሮጀክቱ ከ19 ሚሊየን በላይ የአሜሪካን ዶላርና ከ100 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የሚደረግ ሲሆን ወጪው በአፍሪካ ልማት ባንክና በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈን ይሆናል፡፡
የፕሮጀክቱ ስራ ከ2014 ዓ.ም ጀምሮ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ፕሮጀክቶች ፖርትፎልዮ ማኔጅመንት አማካኝነት እየተከናወነ የሚገኝ ሲሆን እስካሁን ባለው ሂደት ለፕሮጀክቱ የሚያስፈልጉ 4,929 ፖሎች ተመርተዋል፡፡
በአፍዴራ ሳይት 469 የመካከለኛ ቮልቴጅ መስመር ምሰሶ ተከላ ተከናውኗል፡፡ በተጨማሪም ለግንባታው የሚያስፈልጉ ከውጭ ሃገር የገቡ ኮንዳክተር፣ ኢንሱሌተርና ሌሎች ግብዓቶች ፍተሻ ተከናውኗል፡፡
በግንባታ ሂደት ያጋጠሙ ችግሮችን ለመፍታት ከአፋር ክልል ውሃና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊዎች ጋር ምክክር በማድረግ መዋቅራዊ አሰራር ማስቀመጥ መቻሉን ለማወቅ ተችሏል፡፡
ፕሮጀክቱን በዚህ ዓመት ለማጠናቀቅ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ ይገኛል፡፡
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
በአፋር ክልል ለሚገኙ የጨውና ፖታሽ አምራች ኢንዱስትሪዎች እንዲሁም 38 የገጠር ከተሞችና መንደሮች የ24 ሰአት የኤሌክትሪክ አገልግሎት ለማቅረብ እየተሰራ ነው፡፡
ለፕሮጀክቱ ከ19 ሚሊየን በላይ የአሜሪካን ዶላርና ከ100 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የሚደረግ ሲሆን ወጪው በአፍሪካ ልማት ባንክና በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈን ይሆናል፡፡
የፕሮጀክቱ ስራ ከ2014 ዓ.ም ጀምሮ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ፕሮጀክቶች ፖርትፎልዮ ማኔጅመንት አማካኝነት እየተከናወነ የሚገኝ ሲሆን እስካሁን ባለው ሂደት ለፕሮጀክቱ የሚያስፈልጉ 4,929 ፖሎች ተመርተዋል፡፡
በአፍዴራ ሳይት 469 የመካከለኛ ቮልቴጅ መስመር ምሰሶ ተከላ ተከናውኗል፡፡ በተጨማሪም ለግንባታው የሚያስፈልጉ ከውጭ ሃገር የገቡ ኮንዳክተር፣ ኢንሱሌተርና ሌሎች ግብዓቶች ፍተሻ ተከናውኗል፡፡
በግንባታ ሂደት ያጋጠሙ ችግሮችን ለመፍታት ከአፋር ክልል ውሃና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊዎች ጋር ምክክር በማድረግ መዋቅራዊ አሰራር ማስቀመጥ መቻሉን ለማወቅ ተችሏል፡፡
ፕሮጀክቱን በዚህ ዓመት ለማጠናቀቅ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ ይገኛል፡፡
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት