ከብልሹ አሰራር የፀዳ ተቋም መፍጠር የሁሉም ሃላፊነት ነው
ከብልሹ አሰራር የፀዳ ተቋም መፍጠር በየደረጃው የሚገኘው አመራርና ሰራተኛ ሃላፊነት መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ ሽፈራው ተሊላ (ኢ/ር) ገልፀዋል፡፡
ዋና ስራ አስፈጻሚው የምክክሩን መድረክ ማጠቃለያ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ተቋሙ የጀመረውን የአሰራር ስርዓት ውጤታማ በማድረግ እየጨመረ የመጣውን ሃይል ፍላጎት መመለስ እና የሃገሪቱን ኢኮኖሚ ሊሸከም የሚችል አገልግሎት መስጠት ይገባል ብለዋል፡፡
ከብልሹ አሰራር የፀዳ፣ ስልጡንና አገልጋይ አመራርና ሰራተኛ በመፍጠር ጥራት ያለውና አስተማማኝ የኤሌክትሪክ አገልግሎት መስጠት እንደሚገባ ኢ/ር ሽፈራው አሳስበዋል፡፡
የተጠያቂነት ስርዓት በመዘርጋት የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መቅረፍ እንደሚገባ የገለፁት ዋና ስራ አስፈጻሚው የብልሹ አሰራር ችግር በሚታይባቸው አመራርና ሰራተኞች ላይ ተገቢ የሆነ እርምጃ መውሰድ እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡
ለደንበኞች የሃይል ጥያቄ ፈጣን ምላሽ በመስጠት፣ የቅሬታ ምንጮችን በማድረቅ እና ፈጣን ምላሽ በመስጠት የደንበኞችን የእርካታ ደረጃ ማሳደግ እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡
በተጨማሪም ኢ/ር ሽፈራው በፕሮጀክቶች አፈጻፀም ላይ ተገቢ ክትትልና ቁጥጥር በማድረግ እና የባለድርሻ አካላትን ተሳትፎ በማሳደግ የኤሌክትሪክ ተደራሽነት እውን ማድረግ እና በገጠሩ የሃገራችን ክፍሎች የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ማድረግ ይገባል፡፡
በመጨረሻም ዋና ስራ አስፈጻሚው የታዩ ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በመለየት ችግር ፈች የሆኑ የፈጠራ ስራዎችን በማከናዎን የተቋሙን አቅም ማሳደግና በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ተቋም መፍጠር ይገባል ብለዋል፡፡
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
ከብልሹ አሰራር የፀዳ ተቋም መፍጠር በየደረጃው የሚገኘው አመራርና ሰራተኛ ሃላፊነት መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ ሽፈራው ተሊላ (ኢ/ር) ገልፀዋል፡፡
ዋና ስራ አስፈጻሚው የምክክሩን መድረክ ማጠቃለያ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ተቋሙ የጀመረውን የአሰራር ስርዓት ውጤታማ በማድረግ እየጨመረ የመጣውን ሃይል ፍላጎት መመለስ እና የሃገሪቱን ኢኮኖሚ ሊሸከም የሚችል አገልግሎት መስጠት ይገባል ብለዋል፡፡
ከብልሹ አሰራር የፀዳ፣ ስልጡንና አገልጋይ አመራርና ሰራተኛ በመፍጠር ጥራት ያለውና አስተማማኝ የኤሌክትሪክ አገልግሎት መስጠት እንደሚገባ ኢ/ር ሽፈራው አሳስበዋል፡፡
የተጠያቂነት ስርዓት በመዘርጋት የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መቅረፍ እንደሚገባ የገለፁት ዋና ስራ አስፈጻሚው የብልሹ አሰራር ችግር በሚታይባቸው አመራርና ሰራተኞች ላይ ተገቢ የሆነ እርምጃ መውሰድ እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡
ለደንበኞች የሃይል ጥያቄ ፈጣን ምላሽ በመስጠት፣ የቅሬታ ምንጮችን በማድረቅ እና ፈጣን ምላሽ በመስጠት የደንበኞችን የእርካታ ደረጃ ማሳደግ እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡
በተጨማሪም ኢ/ር ሽፈራው በፕሮጀክቶች አፈጻፀም ላይ ተገቢ ክትትልና ቁጥጥር በማድረግ እና የባለድርሻ አካላትን ተሳትፎ በማሳደግ የኤሌክትሪክ ተደራሽነት እውን ማድረግ እና በገጠሩ የሃገራችን ክፍሎች የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ማድረግ ይገባል፡፡
በመጨረሻም ዋና ስራ አስፈጻሚው የታዩ ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በመለየት ችግር ፈች የሆኑ የፈጠራ ስራዎችን በማከናዎን የተቋሙን አቅም ማሳደግና በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ተቋም መፍጠር ይገባል ብለዋል፡፡
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት