EOTC ቤተ መጻሕፍት


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: не указана


ይህ Channel የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ያን የሆኑ ቅዱሳት መጻሕፍት፤ ስብከትች እንዲሁም የተለያዩ ለአብነት ትምህርት የሚሆኑ በድምፅ ፤ይሁን በጹሁፍ እንዲሁም በ Video ሚለቀቅበት Channl new
ተጨማሪ ወይም ሚፈልጉትን መፃህፍት
ብለው ይጠይቁን
ማስታወቂያም እንሰራለን በውስጥ መስመር ይጠይቁን
የሰማነዉን እንናገራለን!
ያየነዉን እንመሰክራለን!

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
не указана
Статистика
Фильтр публикаций


'https://t.me/addlist/2CQ3e4ZJYT9hZGNk' rel='nofollow'>🟢መናፍቃን ከሚያነሷቸው 3 ጥያቄዎች መካከል
1)የጌታችን እኔት የአዳም የውርስ ኃጢአት/ጥንተ አብሶ/አለባት።
2)የጌታችን እናት አልተነሳችም
3)እየሱስ ክርስቶስ አማላጅ ነው።
👉ለነዚህ ጥያቄዎች እና ለመሳሰሉት መልስ የሚያገኙበት ቻናል ነው።አሁኑኑ ይቀላቀሉ።


'https://t.me/addlist/2CQ3e4ZJYT9hZGNk' rel='nofollow'>♥️🌹ጋብቻ ምን ማለት ነው⁉️🌹
ጋብቻ እና የዘር ሐረግ ምን ያገናኛቸዋል⁉️
ጋብቻ የሚፈቀደው ከስንት ዓመት ጀምሮ ነው⁉️
ሴት ሙሽራ ከወንድ ሙሽራ ቀኝ ለምን ትሆናለች⁉️
🌹ሙሽሮች በጫጉላ ጊዜያቸው ለምን አይጾሙም⁉️
ያገባሁት ሰው ካልተመቸኝ ብፈታው ምን ችግር አለው⁉️
እንደምንጋባ እርግጠኛ ከሆንን ግብረስጋ ግንኙነት ብንፈጽም ምን ችግር አለው⁉️
















የ የካቲት 16 የኪዳነ ምረት ስርዓተ ማህለት እነሆ


እግዚአብሔር ለምን ዝም ይላል?
             
Size:-82.9MB
Length:-1:38:35

    በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ

@kendilebirihan
@kendilebirihan
@kendilebirihan


እንደ ሁኔታው ለብቻው ልመለስበት እችላለሁ) በጣም የተለያዩ ሀሳቦች ናቸው። እንዲህ ያለው ችግር ቀደም ብሎም የነበረ ችግር ነው። ስለዚህ አሁንም ለመርታት በሚፈልግ ልቡና ውስጥ ሆኖ ጥቅሶችን ከዐውዳቸው ነጥሎ አውጥቶ መጠቀም ችግርን ያባብስ እንደሆን እንጂ መፍትሔ ሊሆን አይችልምና ከዚህም መጠበቅ ተገቢ ነው።

4) ከመጠራጠር አለመጀመር

መና/ፍቃን ሀሳብ እና ጥያቄ ሲያነሱ የእነርሱን አመክንዮ እና ፍረጃ ሰምቶ ነባር ትምህርቶችን ወይም ምንጮቻችን ከመጠራጠር መጀመር በጣም አደገኛ ነገር ነው። ለምሳሌ ሳጥናኤል እኔ ፈጠርኳችሁ ባለ ጊዜ በጥርጥር የጀመሩት እውነት በተገለጠ ጊዜ ከእርሱ ጋር አብረው ወድቀው የሚያስቱ መናፍስት ሆኑ እንጂ ሲመለሱ አላየናቸውም። እውነቱን ባያውቁም በያለንበት እንቁም ባለው በቅዱስ ገብር ኤል ቃል ጥርጥሩን ሳያስገቡ የጸኑት ግ ን በኋላ እግዚአብሔር እውነቱን ገልጾላቸዋል። ይህ የመጀመሪያው የፍጥረት ፈተና የሚያስረዳን ከመጠራጠር መጀመር ምን ያህል አደገኛ መሆኑን ብቻ ሳይሆን መንገዱ ዲያብሎሳዊ መሆኑን ነው። በሳይንስ ከመጠራጠር መጀመር ወደ ዕውቀት ይወስዳል ከሚባለው በተቃራኒ በሃይማኖት በመጠራጠር አለመጀመር መሠረታዊ ጉዳይ ሆኖ እናገኘዋለን ማለት ነው።

በዚሁ መንገድ ካየን አንዳንድ የግእዝ ምንጮቻችን ከሌላ ሀገር ምንጮች ስናነጻጽር በቀጥታ ላይገጥሙልን ይችላሉ። ለምሳሌ ያህል ገድለ ጊዮርጊስን ስንመለከት ሰማዕቱን ያሰቃየውን ንጉሥ ዱድያኖስ ይለዋል። በሌላው ሀገር ግን ያሉት ምንጮች በሙሉ ደግሞ ንጉሡን ዲዮቅልጥያኖስ ይሉታል። ይህ በመሆኑ የእኛ ምንጭ ስሐተት ነው ልንል አንችልም። እኔ እንኳ በአቅሜ በአደረግሁት ፍለጋ አንድ ጥናት ላይ የጥንት ምንጮች ዱድያኖስ ይሉ እንደነበር አግኝቻለሁ። ስለዚህ ይህ ስም ምንጫችን ስሐተት መሆኑን ሳይሆን ምንጫችንን ወይም አቀባይ ቋንቋችንን እንድንመረምር እና የእኛ ቅጂ ከቀዳማውያን ምንጮች መሆኑን ይጠቁማል እንጂ ልዩ መሆኑ ስሕተት መሆኑን ሊያሳይ አይችልም ማለት ነው።

በገድለ ተክለ ሃይማኖት ላይ ያለው የሞቱበትን በሽታ እንደመስቀሌ እቆጥርልሃለሁ የሚለውን ሀሳብ ስሑታኑ ባነሡበት መንገድ ተመልክቶ ከመጠራጠር ከመጀመር ወደ ገድሉ ጠልቆ ገብቶ ምክንያቱን ከማጥናት መጀመር ከብዙ በሽታ ይፈውሳል። በዚሁ ጉዳይ ላይ ገድሉን ስንመለከት አቡነ ተክለ ሃይማኖት ትልቁ ፍላጎታቸው የደም ሰማዕትነትን ማግኘት ነበር። ዘመኑ ደግሞ ያንን አልፈቀደላቸውም። ስለዚህ ጌታ በበሽታ የገጠማቸውን ተጋድሎ እንደ ሰማዕትነት ወይም መስቀል እንደሚቆጥርላቸው ቃልኪዳን ገባላቸው ይላል እንጂ መና/ፍቃኑ የሚሉትን ወይም ሊሉ የሚፈልጉትን ገድሉ በፍጹም አይልም።

በገድለ ቅዱሳንና በገድለ ቅዱሳን መጽሐፍ መካከል ልዩነት እንኳ ቢኖር ወደ ቀዳማይ ምንጭ በሚደረግ ጥናት ይስተካከላል እንጂ ገድለ ቅዱሳንን ወደ መጠራጠር ሊወስድ አይችልም። በርግጥ የሰው አእምሮ ውሱን ስለሆነ ለእንዲህ ያለ ፈተና ተደጋግሞ ሊወድቅ ይችላል። እንዲህ ያሉትን ነገሮች ደግሞ መጽሐፍ ቅዱስም ያስረዳል። ለምሳሌ ያህል በሰማርያ እጅ ከባድ ረሀብ ተነሥቶ ሁለት ሴቶች ልጆቻቸውን ቀቅለው ለመብላት ከተስማሙና የአንዲቱን ከበሉ በኋላ ሁለተኛ ልጇን ስትደብቅ በተፈጠረው ክርክር ንጉሡ ስሞቶ በኤልሣዕ ላይ ተቆጥቶ ነበር። በኋላ ላይ ግን “የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ፤ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ነገ በዚህ ጊዜ በሰማርያ በር አንድ መስፈሪያ መልካም ዱቄት በአንድ ሰቅል፥ ሁለትም መስፈሪያ ገብስ በአንድ ሰቅል ይሸመታል አለ። ንጉሡም በእጁ ተደግፎ የነበረ አለቃ ለእግዚአብሔር ሰው መልሶ፦ እነሆ፥ እግዚአብሔር በሰማይ መስኮቶች ቢያደርግ ይህ ነገር ይሆናልን? አለው። እርሱም፦ እነሆ፥ በዓይኖችህ ታየዋለህ፥ ከዚያም አትቀምስም አለ” /2ኛ ነገ 7/ ተብሎ እንደተጻፈ ንጉሡ በመጠራጠሩ ምክንያት በሕይወቱ እንዲቀጣ ሆኗል። ስለዚህ ከመጠራጠር መጀመር ውጤቱ አደገኛ መሆኑን መረዳት እና በእምነት ጸንቶ የማያውቁትን ለማውቅ መጣር ተገቢነት ይኖረዋል ማለት ነው። ለዛሬው በእነዚሁ ልፈጸም። ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤ አሜን

©ዲያቆን ብርሀኑ አድማስ
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery


ስለ ሃይማኖታዊ ውይይት አንዳንድ ነገሮች

ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በማኅበራዊ ሚዲያው ሃይማኖታዊ ክርክሮች በረከት እያሉ መጥተዋል። እነርሱን ተከትሎ ደግሞ በአንድ ቤት ውስጥ ባሉትም መካከል ውይይቶች አለፍ ሲልም መነቃቀፎች አንዳንድ ጊዜም ደግሞ በእወቀትም ይሁን ያለዕውቀት መጠላለፍ የሚመስሉ ሁኔታዎች እንዳሉ ይታያል። በእንዲህ ያለው ጊዜ ማድረግ የሚገባን ምንድን ነው የሚሉ ድምፆችም ይሰማሉ። የምናደርገው ነገር በዚህ ጊዜ በዚያ ጊዜ የሚባልበት መሆኑ ባይቀርም በእኔ እምነት በአግባቡ ከተጠቀምንበት እና ከተማርንበት ከሁሉም ልንጠቀም እና መንገዳችንን ትክክል የሆነልን እርሱኑ ልናጸና ፈንገጥ ያልነው ወይም የመንገድ ጠርዝ በመርገጥ የተንሸራተትን ካለንም ልንመለስ እና በመሐል መንገድ እንድንጓዝ ሊጠቅመን ይችላል። እጅግ በትንሹ ከሰማኋቸው ተነሥቼ አጠቃላይ መርሕ ተኮር ሁኔታዎች በዚህ ጽሑፍ ልጠቁምና እንዳስፈላጊነቱ ደግሞ በመከራከሪያ ነጥቦቹም ላይ ላክል እችላለሁ። ከዚህ በፊት “አድማሱ ጀንበሬ ሕይወቱ እና ትምህርቱ” የሚለው መጽሐፍ ሲታተም በመቅድምነት የወጣ አጭር ጽሑፍ ላይ ከንባቦቼ ከቀራረምኩት የተወሰኑ ሀሳቦችን ማጋራቴ ይታወቃል። እነዚያን ያላየ ቢያያቸው አንድ ነገር እንኳ የሚጠቅም ሊያገኝ ይችላል ብዬ አምናለሁ። እነዚያን ያነሣሁበት ምክንያት ግን እነዚህን ጉዳዮች የእነዚያ ቀጣይ አድርጋችሁ እንድትወስዷቸው ለማሳሰብ ያህል ነው።

በውይይትም ሆነ በክርክር ውስጥ ያለን አገልጋዮች ልንጠነቀቅባቸው የሚገቡን ጉዳዮች መካከል

1) በራስ ማስተዋል አለመደገፍ

በመጽሐፍ ቅዱስ ቅዱስ ከተጻፉት ታሪኮች፣ ምክሮች እና ትርጓሜዎች መካከል አንደኛው በራሳቸን መረዳት፣ ማስተዋል (reasoning) ላይ እንዳንደገፍ እና በዚህ ምክንያት ወደ ፈተና እናዳንገባ መጠበቅን የሚመለከት ነው። ለምሳሌ ያህል ያዕቆብ ከዔሳው ብኩርናውን የወሰደበትን ሒደት ስንመለከተው በምንም ዓይነት ተፈጥሮአዊ አመክንዮ ይሠራል ይሆናል ለማለት የሚቻል አይደለም። የአብርሃምና ሣራ እንዲሁም የዘካርያስ እና የኤልሳቤጥ በዕርጅና ልጅ መውለድ የሚያስተምረንም ይህንኑ ነው። ዋናው ጉዳይ ግን እግዚአብሔር እርሱ ባወቀ ኤሳው ቀድሞ እንዳይወለድ እና ያዕቆብ ቀድሞ እንዲወለድ ማድረግ እየቻለ ከተወለደ በኋላ በኩርናውን እንዲወስድ ለምን አደረገ? ለእነ አብርሃም እና ለእነ ዘካርያስ ልጆችን ቀድሞ ለምን አልሰጣቸውም ብለን ብንጠይቅ ዋናው መልስ እግዚአብሔር ሊያስተምረን የፈለገው ከተፈጥሮ ሕግ እና ከየትኛውም አመክንዮ ወይም የሰው የሕሊና መረዳት የሚያልፉ ነገሮችን የሚያደርግ መሆኑን ለማሳየት ነው። በመጽሐፍም “በፍጹም ልብህ በእግዚአብሔር ታመን፥ በራስህም ማስተዋል አትደገፍ፤” /ምሳ 3 ፡ 5/ ተብሎ የተጻፈው ለዚህ ነው።

በርግጥ ሃይማኖት የሚባለውም ይህ ነው። ከመረዳታችን እና ከሎጂካችን ባሻገር እግዚአብሔር የሠራውንና የሚሠራውን ማመን። ጌታችን ከእመቤታችን ከንጽሕት ቅድስት ድንግል ማርያም የተጸነሰበት፣ የተወለደበት፣ የሞተበት፣ ድኅነታችን የፈጸመበት፣ የእመቤትችን በሁለንተና ንጽሕት መሆን እና የመሳሰሉትን ነገሮች መረዳት የሚቻለው ያዕቆብ ከዔሳው ብኩርናውን በወሰደበት መንገድ ብቻ ነው። ይህም ማለት ከሎጂክና ከአመክንዮ ተላልቅቆ እግዚአብሔር አምላክነቱን በየዘመኑ ትውልድ እግዚአብሔርነቱን የገለጸባቸውንና በአእምሮ ከመታሰብ፣ በሎጂክ ከመረዳት በላይ የሆኑትን በመቀበል ነው። ያዕቆብ ብኩርናን የወሰደበት መንገድ በእምነት የምንቀበለው ብቻ ነውና። እነዚህ ነገሮች የተፈጸሙት፣ እና በቅዱሳት መጻሕፍት የተመዘገቡበት ዋና ዓላማም የአካላዊ ቃል ሰው መሆን ጋር ተያይዞ ለሚነሱ ጥያቄዎች በሙሉ አስቀድመው የተዘጋጁ መልሶች እንዲሆኑ ነው።

በራስ ማስተዋል ወይም በራስ የመረዳት ችሎታ ላይ መደገፍ ቢያንስ ሁለት ታላላቅ ፈተናዎችን ወደ እኛ ያመጣል። የመጀመሪያው ከእምነት መጉደል ነው። ይህ ደግሞ እንኳን በእኔ ቢጤዎች ይቅርና ጻድቁ ዘካርያስንም ፈትኖታል። ዘካርያስ ቅዱስ ገብርኤልን የተከራከረው ዕውቀት ወይም የተፈጥሮ ሕግ ገድቦት ነውና። ሰው ካረጀ ካፈጀ በኋላ አይወልድም የሚለው ዕውቀቱ ወይም የተፈጥሮ ሕጉ ስሕተት ሆኖ አልነበረም። የእግዚአብሔር የማዳን ሥራ ግን ከእነዚህ የሚያልፍ ነበረ። ስለዚህ በመረዳት ወይንም በማስተዋላችን ላይ መደገፍ መጀመሪያ የሚያመጣው ፈተና እንኳን ሰዎች መላእክትም ቢናገሩን እንድንከራከር ሊያደርገን ይችላል ማለት ነው። ሌላው ቀርቶ ትናንት ያከበርነው የልደተ ስምዖን ታሪክ የሚያስታውሰንም ይህንኑ ገጠመኝ ነው። ሴት እንጂ ድንግል አትወልድም የሚል ሀሳብ ይዞ ድንግል ትጸንሳለች የሚለውን የነቢዩን የኢሳይያስን ቃል ሴት ወደሚል ለመቀየር ሞክሮ ከእግዚአብሔር ይህን ሳያይ እንዳይሞት የተረዳው የእግዚአብሔር አሠራር ከሰው ማስተዋል እና መረዳት ባሻገር ስለሆነ ነው። በዚህች መንገድ መጓዝ የጀመረ ሰው አይሁድ ከመስቀል ውረድና እንመንብህ እንዳሉት በራስ መረዳት ቅድመ ሁኔታ አስቀመጦ እግዚአብሔርን መፈተኑ የማይቀር ነው።

ሁለተኛው እና ከባዱ ፈተና ደግሞ ሌሎች ይህን መረዳት እንደማይችሉ በማሰብ የዲያብሎስ ረቂቅ ወጥመድ በሆነው የትዕቢት ወጥመድ ውስጥ መውደቅን ሊያስከትል ይችላል። ይህ ደግሞ ብዙ ጥፋቶችን አከታትሎ ያመጣብናል። ሰሎሞን “በልቡ የታበየ ሁሉ በእግዚአብሔር ዘንድ ርኩስ ነው፥ እጅ በእጅም ሳይቀጣ አይቀርም” /ምሳ 16 ፡ 5/ ሲል እንደገለጸው ቅጣቱም ቀጥታ ከእግዚአብሔር ይሆናል። ለሰውየው ግን እያወቀ ወይንም እውቀቱ ትክክል ስለሆነ እንጂ እየታበየ እና እየተጎዳ እንደሆነ አይሰማውም። ለዚህም ነው “ለሰው ቅን የምትመስል መንገድ አለች፤ ፍጻሜዋ ግን የሞት መንገድ ነው” /ምሳ 16 ፡ 25/ ተብሎ የተጻፈው ። ስለዚህ ከሁለቱም ለመጠበቅ በራስ መረዳት ላይ አለመደገፍ ትልቁ መፍትሔ ነው። የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች እና ምክሮች ያረጋገጡልንም ይህንኑ ነው።

2) ከትዕቢት / ካለመሸነፍ መንፈስ መራቅ

የትዕቢት ነገር ከላይም የተጠቆመ ቢሆንም በዓለም ለተፈጠሩት ችግሮች ሁሉ መሠረቱ ትዕቢት ነው። በተለይ በሰው ፊት ተሸናፊ መባልን፣ አያውቅም መባልን መፍራት፣ ተሳስቷል መባልን መሸሽ ወደ ማስረዳት እና ራስን ነጻ ለማውጣት ሲባል ወደ ተለጠጠ ክርክር ይስባል፣ ከዚያም ወደ ባሰው ችግር ወይም ፈተና ሊያደርስ ይችላል። ስለዚህ ጥያቄዎች ሲፈጠሩ ቆም ብሎ ማድመጥ ፣ መጸለይ እና ቅዱሳት መጻሕፍትን እያጠኑ ሊቃውንትን ደጋግሞ መጠየቅ ብዙ ችግሮችን ያስወግዳል። ይልቁንም ልሳሳት እችላለሁ በሚል ትሑት ሰብእና ውስጥ ሆኖ እግዚአብሔርን የሚለምን ሰው እግዚአብሔር በፍጥነት ከዚህ ችግር እንደሚያወጣው የታመነ ነው።

3) የምንጮችን ዐውድ በአግባቡ ለመራዳት መጣር

ብዙ ጊዜ ወደ ክርክር ተይዘው የሚወጡት ምንጮች ወይም ማስረጃዎች በራሳቸው ምንም ችግር የለባቸውም። ሆኖም ከተነገሩበት ወይም ከተጻፉበት ዐውድ አውጥተን ከተመለከትናቸው ችግር ውስጥ ልንወድቅ እንችላለን። ለምሳሌ ያህል ጥንተ አብሶን በተመለከተ የሚነሣው ክርክር ለዚህ ጥሩ ምሳሌ ሊሆን ይችላል። የጥንት ሊቃውንት ጌታ ሥጋውን ከሰማይ ይዞ ወርዷል፣ በእመቤታችን አደረባት እንጂ ሥጋን ከእርሷ አልነሣም ለሚሉ የዚያ ዘመን መና/ፍቃን የተሰጡ መልሶች ያንኑ የበደለውን ሰው የአዳምን ሥጋ ነው የተዋሐደ ሲሉ ያንን የሳተውን፣ የወደቀውን፣ የጎሰቆለውን የእዳም ሥጋ እንደተዋሐደ ተከራክረው አስረድተዋል። ሆኖም እነዚህ አገላለጾች እመቤታችንን ጥንተ አብሶ አለባት ሊያስብሉ አይችሉም። (ይህን ጉዳይ


፩ኛ፦ ጠንቅቀን በማናውቀው ጉዳይ ላይ መናጆ/አንጃ ሆነን አስተያየት አለመስጠት መልካም ነው።

፪ኛ፦ የዕውቀታችንን ምንጭ መመርመር መልካም ነው። ከልምድ ነው? ከመጽሐፍ ነው? ከመምህር ነው? ከመሰለኝ ነው? ከምንድን ነው?

፫ኛ፦ የሰውን አለማወቅ እንደ Advantage ተጠቅሞ ማታለል አይገባም። ለምሳሌ ማንኛውም ክርስቲያን ንስሓ ገብቶ ሥጋውን ደሙን መቀበል ይገባዋል። ወደ ገጠር ስንሄድ ግን ወጣት አይቆርብም እያሉ አንዳንድ ሰዎች ሲከለክሉ ይስተዋላል። ይህ ስሕተት ነው። አንዱ መምህር ሄዶ ንስሓ እየገባችሁ ሥጋውን ደሙን ተቀበሉ ቢል ሰው ከልምዱ ተነሥቶ ሊጠላው ይችላል። የተናገረው ግን እውነት ነው። ሌላ እወደድ ባይ መምህር አዎ ወጣት መቁረብ የለበትም ብሎ ሕዝቡ የሚያቀርባቸውን አመክንዮዎች ቢያቀርብ ሕዝቡ ደስ ሊለው ይችላል። ሕዝቡም የዚህ ደጋፊ ሊሆን ይችላል። መማር እንደዚህ ነው ሊልህ ይችላል። እውነታው ግን የላይኛው ነው። በዚህ ጊዜ ከሕዝቡ የሐሰት ፈጠራ ይልቅ እግዚአብሔራዊውን እውነት ተናግሮ ከመሸበት ማደር ይገባል።

፬ኛ፦ ፈሪሳዊነትን እናስወግድ። ፈሪሳውያን በእግዚአብሔር ቃል ላይ የራሳቸውን ወግ እየጨመሩ ያስተምሩ ነበር። ለወጋቸው መጽሐፋዊ ወይም ቅዱስ ትውፊታዊ የሆነ ማስረጃ የላቸውም። ግን ሕዝቡ ወጋቸውን እንደ ጽጽቅ እንዲያይላቸው ይጥሩ ነበር።

፭ኛ፦ ክፉ ነገሮችም፣ መልካም ነገሮችም በትውፊት ከትውልድ ወደ ትውልድ ሊተላለፉ ይችላሉ። እኛ ቅዱስ ትውፊትን መቀበል አለብን። ቅዱስ ትውፊት በመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ላይ የተመሠረተ ነው። ከመጽሐፍ ቅዱስ አስተምህሮ የሚቃረን ከሆነ ትውፊት ቢሆንም እንኳ ቅዱስ ትውፊት ስላልሆነ አንቀበለውም።

፮ኛ፦ እግዚአብሔር ልብን የሚመረምር ስለሆነ ከእያንዳንዱ ሐሳባችን፣ ንግግራችን፣ ተግባራችን ጀርባ ያለውን ጉዳይ መመርመር ይገባናል። ከፍቅር ተነሥተን ነው? ከጥላቻ ተነሥተን ነው? ለሃይማኖታችን ከማሰብ ነው? ከአንጃነት ነው? ከምቀኝነት ነው? ከቅንዐት ነው? እግዚአብሔርን ከመውደድ ነው? በጠቅላላው ልባችንን እንፈትሽ። በእያንዳንዱ ንግግራችን፣ በእያንዳንዱ ሐሳባችን፣ በእያንዳንዱ ተግባራችን በእግዚአብሔር ፊት እንመዘንበታለንና።

፯ኛ፦ አንዳንዱ ሊሳደብ፣ ክፉ ስም ሊሰጥ ይችላል። አንዳንዱ ደግሞ ሊዋሽ ይችላል። በዚህ ጊዜ ስድቡን ቸል ብሎ ጉዳዩ ላይ ማተኮር መልካም ነው። ታግሠው ሲቀበሉት የበረከት ምንጭ ነውና። (አንዳንዱ የማስረዳት አቅም ሲያጥረው ስድብን እንደ አማራጭ ሊጠቀም ይችላል። ስለዚህ የሰውየውን ድክመቱን መረዳትና ንቆ መተው መልካም ነው)።

፰ኛ፦ ንግግሮችን፣ ጽሑፎችን ከነዐውዳቸው ለመረዳት መጣር ይገባል።

፱ኛ. ሟች መሆናችንን ለአፍታም ቢሆን መዘንጋት የለብንም። መቼ እንደምንሞት ስለማናውቅ ከመሞታችን በፊት መሥራት አለብን ብለን ያሰብነውን ጉዳይ ለመፈጸም መትጋት ይገባናል።

፲ኛ፦ አጥፍተን ከነበረ ይቅርታ ማለትን እንልመድ። ትሑት ልቡናን ገንዘብ እናድርግ። ፈሪሀ እግዚአብሔርን እናስቀድም።

© በትረ ማርያም አበባው
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery


ጊዜ ለምን? || ጾመ ነነዌ
             
Size:-82.9MB
Length:-1:29:33

    በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot











Показано 20 последних публикаций.