ቅዱሳን በጸሎታቸውና በትምህርታቸው ከርኲሳን መናፍስትና ከጨለማው ልጆች፣ ከክፉ ሰዎች ሽንገላና ተንኰል ለመሰወርና ለመጠበቅ ከእግዚአብሔር የተቀበሉት ሥልጣን ምንጊዜም ይሠራል፡፡ የጻድቃንን ስም ጠርቶ እግዚአብሔርን በመለመን በረከትና ረድኤት ይገኛል፡፡ ስለ ጻድቃን ብሎ እግዚአብሔርም ምሕረቱን ያድላል፡፡ ጻድቃንን ማሰብ ሥራቸውን መዘከር ክርስቲያናዊ ሕይወታችንን ያጐለምሳል፤ በነፍስ በሥጋ ይታደገናል፤ ይጠቅመናል፡፡ ስለዚህም ቤተ ክርስቲያናችን ጻድቃንን እንድናስባቸው፣ በስማቸውም ለድኾች እንድንመጸውት፣መታሰቢያቸውን እንድናደርግ የምትመክረን፤ የምታስተምረን /ማቴ.፲፥፵፩-፵፪/፡፡ በዚህም መሠረት ኦርቶዶክሳዊት ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን የጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖትን መጋቢት ፳፬ ቀን ፅንሰታቸውን፣ ታኅሣሥ ፳፬ ቀን ልደታቸውን፣ ጥር ፳፬ ቀን ስባረ ዐጽማቸውን፣ ግንቦት ፲፪ ቀን ፍልሰተ ዐጽማቸውን፣ ነሐሴ ፳፬ ቀን ደግሞ ዕለተ ዕረፍታቸውን በመንፈሳዊ ሥነ ሥርዐት በታላቅ ድምቀት ታከብራለች፡፡
የኢትዮጵያዊው ጻድቅ የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ጸሎታቸው እና አማላጅነታቸው አይለየን፡፡ አሜን፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ዋቤ መጻሕፍት
✍️ ገድለ አቡነ ተክለ ሃይማኖት
✍️ ገድለ አቡነ ኢየሱስ ሞዓ
✍️ መጽሐፈ ስንክሳር
✍️ የቤተክርስቲያን ታሪክ
የኢትዮጵያዊው ጻድቅ የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ጸሎታቸው እና አማላጅነታቸው አይለየን፡፡ አሜን፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ዋቤ መጻሕፍት
✍️ ገድለ አቡነ ተክለ ሃይማኖት
✍️ ገድለ አቡነ ኢየሱስ ሞዓ
✍️ መጽሐፈ ስንክሳር
✍️ የቤተክርስቲያን ታሪክ