አሜሪካ በ #ሱዳን የጦር አዛዥ አአል ቡርሃን ላይ ማዕቀብ ጣለች
አሜሪካ የሱዳን የጦር አዛዥ ጄኔራል አብዱል ፈታህ አል ቡርሃንን በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች የተገደሉበትንና በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች የተፈናቀሉበትን የእርስ በእርስ ጦርነት በማባባስ ከሳለች። የአሜሪካ ግምዣ ቤት፤ የቡርሃን አመራር የሲቪል መሰረተ ልማትን ጨምሮ በትምህርት ቤቶች፣ በገበያዎች እና በሆስፒታሎች ላይ ጥቃቶች መፈጸማቸውን እንዲሁም ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ ግድያ መፈጸማቸውን ገልጿል።
በዚህም ትናልንት በአልቡርሃን ላይ ማዕቀብ የተጣለ ሲሆን ይህም የሱዳኑ ፈጥኖ ደራሽ ኃይል አዛዥ በሆኑት ሞሐመድ ሀምዳን ዳጋሎ ላይ ተመሳሳይ እርምጃ ከተወሰደ ከአንድ ሳምንት በኋላ ነው።
"የቡርሃን አመራር ሰራዊት ከድርድር ይልቅ ጦርነትን መርጧል" ያለው የአሜሪካ ግምጃ ቤት፤ እርምጃው ከቡርሃን ጋር የተያያዙ የአሜሪካን ንብረቶች በሙሉ እንደሚያግድ እና አሜሪካውያን ከእሳቸው ወይም ከተዛመጅ አካላት ጋር እንዳይገናኙ የሚከለክል መሆኑንም አክሎ ገልጿል።
በተጨማሪም ዋሽንግተን የሱዳን-ዩክሬን ዜግነት ያላቸውን እና በሆንግ ኮንግ የሚገኘውን ኩባንያ ጨምሮ የጦር መሳሪያ አቅራቢዎችን ለሱዳን ጦር መሳሪያ በሚያቀርቡ አካላት ላይም ትኩረት አድርጋለች።
የቡርሃን በአልጀዚራ በተላለፈው ንግግራቸው “እቺን ሀገር ለማገልገል ማንኛውንም ማዕቀብ እንቀበላለን" ሲሉ ተደምጠዋል። የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በበኩሉ የአሜሪካን እርምጃ "ግራ የሚያጋባ እና ደካማ የፍትህ ስሜት" ሲል ተችቷል።
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
አሜሪካ የሱዳን የጦር አዛዥ ጄኔራል አብዱል ፈታህ አል ቡርሃንን በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች የተገደሉበትንና በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች የተፈናቀሉበትን የእርስ በእርስ ጦርነት በማባባስ ከሳለች። የአሜሪካ ግምዣ ቤት፤ የቡርሃን አመራር የሲቪል መሰረተ ልማትን ጨምሮ በትምህርት ቤቶች፣ በገበያዎች እና በሆስፒታሎች ላይ ጥቃቶች መፈጸማቸውን እንዲሁም ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ ግድያ መፈጸማቸውን ገልጿል።
በዚህም ትናልንት በአልቡርሃን ላይ ማዕቀብ የተጣለ ሲሆን ይህም የሱዳኑ ፈጥኖ ደራሽ ኃይል አዛዥ በሆኑት ሞሐመድ ሀምዳን ዳጋሎ ላይ ተመሳሳይ እርምጃ ከተወሰደ ከአንድ ሳምንት በኋላ ነው።
"የቡርሃን አመራር ሰራዊት ከድርድር ይልቅ ጦርነትን መርጧል" ያለው የአሜሪካ ግምጃ ቤት፤ እርምጃው ከቡርሃን ጋር የተያያዙ የአሜሪካን ንብረቶች በሙሉ እንደሚያግድ እና አሜሪካውያን ከእሳቸው ወይም ከተዛመጅ አካላት ጋር እንዳይገናኙ የሚከለክል መሆኑንም አክሎ ገልጿል።
በተጨማሪም ዋሽንግተን የሱዳን-ዩክሬን ዜግነት ያላቸውን እና በሆንግ ኮንግ የሚገኘውን ኩባንያ ጨምሮ የጦር መሳሪያ አቅራቢዎችን ለሱዳን ጦር መሳሪያ በሚያቀርቡ አካላት ላይም ትኩረት አድርጋለች።
የቡርሃን በአልጀዚራ በተላለፈው ንግግራቸው “እቺን ሀገር ለማገልገል ማንኛውንም ማዕቀብ እንቀበላለን" ሲሉ ተደምጠዋል። የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በበኩሉ የአሜሪካን እርምጃ "ግራ የሚያጋባ እና ደካማ የፍትህ ስሜት" ሲል ተችቷል።
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ