'ብርጌድ ንሐመዱ' የተሰኘዉ የፕሬዝዳንት ኢሳያስ አገዛዝ ተቃዋሚ ቡድን አዲስአበባ ላይ ቢሮ ሊከፍት ነዉ ተባለ
በውጭ አገራት የተመሠረተው 'ብርጌድ ንሐመዱ' የተሠኘው የኤርትራ ተቃዋሚዎች ስብስብ ኢትዮጵያ ውስጥ በቀጣዮቹ ጥቂት ቀናት ቢሮ ሊከፍት መኾኑን መስማቱን አፍሪካ ኢንተለጀንስ ዘግቧል።
'ብርጌድ ንሐመዱ' ወይም 'የሰማያዊ አብዮት ንቅናቄ' የተሰኘው የለውጥ ፈላጊ ወጣቶች ስብስብ፣ ከአንድ ሳምንት በፊት አዲስ አበባ ውስጥ ስብሰባ ማካሄዱ ይታወሳል።
በዚኹ ስብሰባ ላይ ከተለያዩ የዓለም ክፍሎች የተወከሉ የንቅናቄው አባላት እንደተሳተፉ በወቅቱ ተዘግቦ ነበር።
ንቅናቄው በውጭ አገር የተመሠረተው ከኹለት ዓመት በፊት ሲኾን፣ በተለያዩ የምዕራቡ ዓለም አገራት የኤርትራ ኢምባሲዎችና የመንግሥት ደጋፊዎች ያካሄዷቸውን የባሕል ፌስቲቫሎች በማወክና በማስተጓጎል ይታወቃል። (Via:-ዋዜማ)
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
በውጭ አገራት የተመሠረተው 'ብርጌድ ንሐመዱ' የተሠኘው የኤርትራ ተቃዋሚዎች ስብስብ ኢትዮጵያ ውስጥ በቀጣዮቹ ጥቂት ቀናት ቢሮ ሊከፍት መኾኑን መስማቱን አፍሪካ ኢንተለጀንስ ዘግቧል።
'ብርጌድ ንሐመዱ' ወይም 'የሰማያዊ አብዮት ንቅናቄ' የተሰኘው የለውጥ ፈላጊ ወጣቶች ስብስብ፣ ከአንድ ሳምንት በፊት አዲስ አበባ ውስጥ ስብሰባ ማካሄዱ ይታወሳል።
በዚኹ ስብሰባ ላይ ከተለያዩ የዓለም ክፍሎች የተወከሉ የንቅናቄው አባላት እንደተሳተፉ በወቅቱ ተዘግቦ ነበር።
ንቅናቄው በውጭ አገር የተመሠረተው ከኹለት ዓመት በፊት ሲኾን፣ በተለያዩ የምዕራቡ ዓለም አገራት የኤርትራ ኢምባሲዎችና የመንግሥት ደጋፊዎች ያካሄዷቸውን የባሕል ፌስቲቫሎች በማወክና በማስተጓጎል ይታወቃል። (Via:-ዋዜማ)
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ