👩◈ ሚስቴና አባቷ ◈👴🏻
ክፍል - አምስት [፭]
.
.
.
በዚህ መሀል እኔና ሚሽቴ ካለንበትን ክፍል አባቷ ወደ ተኙበት ክፍል የሚያስገባው መሀለኛው በር የተንጠለጠለው መጋረጃ ገለጥ ሲል እኔም የኔ ተዋቡም እኩል አየነው ድምጣችን ብቻ ታይሆን ትንፋሻችን ጠፋ••••••
የተገለጠው መጋረጇ ወደ ቦታው ቲመለስ አይተውን ተመልሰው ሄደው ተኙ እንዴ? ብዬ ጆሮዬን ትቀስር ማንኮራፋታቸው ድምጡ ቢቀንስም አሁንም ጨርሶ አልጠፋም።
እያንኮራፉ ነው ።እሳቸው ተሆኑ መጋረጃውን የገለጡት ምንግዜ ተኝተው ምንግዜ ማንኮራፋታቸውን ቀጠሉ እያልሁ በመሀል ወደ ክፋሉ ወለል ትመለከት መጋረጃውን እንደሰው ገልጦ የገባው
ያ ጥላሸት የመሰለ የተዋቡ ድመት ሽቅብ እያየዪ ይንጠራራል።
ደንግጣ ወደ እምትቁለጨለጨው ተዋቡ ጆሮ ጠጋ አልሁን
"ኤድያ ቆሌውን ይግፈፈውና ያ ሻንቅላ ድመትሽ ነው ባክሽ ቄሌያችንን የገፈፈው እሄው እታች ቆሞ እየገላመጠኝ ይንጠራራል ፣ እኔማ አንዳንዴ አስተያየቱን ስመለከት እንደማልወደው ልቡ የነገረው እኮ ነው የሚመስለኝ ።
መጥቶ አጠገብሽ ሊተኛ አስቧል መሰል ሄዶ ላባትሽ ተማቃጠሩ በፊት ቦታ ልልቀቅለት "
ብያት በገዛ ቤቷ እንደልቧ የመሳቅ መብቷን የተነጠቀይው ተዋቡ ታፈናት ሳቅ ጋር ትትታገል እኔ ተነስቼ በገባሁባት መስኮት ወደ ክፍሌ ተመለስሁ።
መስኮቷን ስዘጋት ቅድም ትከፍታት ተጮኸችው በላይ
"ቀርርርርርርር እያለይ ትትጮህ ተሳቀኹይ ኧረ እሚያሳቅቅ ነገር ያሳቆት አቦ
ተዋቡ አቅሏን ስታ ስትጬህ አፏን አፈንኋት ይችን መስኮት ምኗን ላፍናት እናንተው?"
ጥርሴን መንከሴ ተጩኸት ያስጥላት ይመስል ጥርሴን ነክሼ ዘጋኋትና "ነግቶ ተዋቡ ትትነሳ ተውስጥ ትሸጉረዋለይ " እያልሁ ታጣፊዋ አልጋዬን ቁልቁል ታያት አስጠላችኝ።
በላብ ተሚያጠምቅ የፍቅር እሳት ተሚዘንብበት አልጋ ላይ አውርደህ በረዶ ላይ ያስተኛኸይ የተዋቡ አባት የስራህን ይስጥህ ብዬ ሽቅብ ተራገምሁና ተጠቅልዬ ተኛሁ።
ተሁለት ቀን ቡሀላ ዳግም መስኮቷን ከፈተችልይ። ተመግባቴ በፊት
"አባቷ ሰማ አልሰማ እያልሁ ታልሳቀቅ አልጋውንም ተዋቡንም እያስጮሁክ ታሰኛይ እኔም እየጮሁክ የልቤን በማድረስ አባቷ በብስጭት በውድቅት ለሊት በሮ እንዲጠፋ ታላረግሁ እኔ አንዳርጌ አይደለሁም !!"
ብዬ ፈክሬ ገባሁ። ተገባሁ ኋላ ግን ተዋቡ "ተው ቀስበል አለሜ አብዋ እንዳይሰማ !"
እያለይ ስለምነይ ለሷ ትል ተውሁት። አቧቷ በመሀል ድንገት ማንኮሯፋቱን አቁሞ መገላበጥ ቲያበዛ ተዋቡ •••
"ታይሰማን አይቀርም!" ብላ በጭንቀት ነፍሷ ልትወጣ ደረሰይ። እኔም የሷ ጭንቀት ትላስጨነቀይ በመሀል አቋርጬ ድምጣችንን አጥፍተን ትንሽ ቆየንና መገላበጡን አቁሞ ማንኮራፋት ቲጀምር ተነስቼ ወደክፍሌ ተመለስሁ።
ተስድስት ቀን በላይ በግዜ እየገባሁ እክፍሌ እያመሸው ብቆይም አባቷ ሀሳባቸውን ለመቀየር ፍንጭም ታያሳዩ ስለቆዩ ተበሳጨሁ።
እኝህ ሰው በምን ብልሀት ተኔም ተሚሽቴም አናት ላይ ሊወርዱ እንደሚችሉ ቁጭ ብዬ ታሰላስል ዋልሁ። አንድ ሀሳብ ስለመጣልይ ተዋቡ ማታ እራት ይዛ ክፍሌ ትትመጣ ያሰብሁትን ነገርዃት።
ምን አሰብሁ መሰለሽ ውብ አለሜ እኔ ሆን ብዬ ታምሚያለሁ ብዬ እተኛለሁ ። ያኔ አንቺ እንደተጨነቅሽ ሆነሽ •••
"እንዲህ ታሞማ ብቻውን እይህ ክፍል ውስጥ መተኛቱ ደግ አደለም እላይ ቤት ተኝቶ ላስታመው እይ ብለሽ ሀሳብ ታቀርቢያለሽ ።
መቼስ ሰው ናቸውና ታምሜ እያዩ አይሆንም አይሉም አደል?" ስላት።
"ኧረ አይልም አባዬ እኮ እንደሀይለኝነቱ ሁሉ ሩህሩህ ነው !" አለይ።
"ደግ እንግዲህ አንዴ እላይ ቤት ተገባሁ ቡሀላ ተሻለኝም አልተሻለኝም እይህ የሚቀመጡበት ምህንያት ስለማይኖራቸው መሄዳቸው አይቀርም"
"ልክ ብለሀል! አወይ አለሜ እንደው ምን ስትል እሄን መላ አሰብኸው በል !
ታብዋ ጋር ታንቀያየም በሰላም ችግራችንን የምንፈታበት ብልህ መላ ነው።
በል ነገ ተምኝታህም ሳትነሳ የታመምህ መስለህ ተኛ!" ብላይ ወጣይ።
አባቷ ጥዋት ጥዋት እኔ ታለሁባት ክፍል በር ላይ ጠሀይ እንደሚሞቁ አውቃለሁ ። ተንቅልፌ ቀደም ብዬ ብነቃም ሰአታቸው እስክትደርስ እዛው ትገላበጥ ቆየሁ።
ሁለት ሰአት ላይ ተምኝታዬ ተነስቼ በበሩ ፍንጭት ወደ ውጪ አጮለቅሁ።
እተለመደው ቦታ በርጬማቸው ላይ ተቀምጠው ጠሀይ እየሞቁ ዳዊት ቲደግሙ አየኋቸው••••
"ተሀምሳ ዳዊት የልብ ቅንነት" አለይ እምዋ
የኛን ትዳር እያሳመሙ ዳዊት ቢደግሙ ምን ዋጋ አለው።
ለሊቱን አብረን እንዳንሆን መከልከላቸው ታያንስ ቀንም እንደወንድ ወጣ ብለው ስለማይመለሱ እምንገናኝበትን ቀዳዳ ሁሉ ደፍነው በናፍቆት ርሀብ እየቀጡን ዳዊት ትለደገሙ ተቅጣት የሚያመልጡ መሰላቸው እንዴ?
ተመጡ ጀምሮ የለሊቱ ይሁን ቀን እንኳን ተቤት አይወጡም እኮ እናንተው
ተሁለት እስተ አራት ሰአት ጠሀይ ቲሞቁ ይቆያሉ ።
ጠሀይዋ አየል እያለይ ትትመጣ ተነስተው ግቢ ውስጥ ወዳለ አንድ ትልቅ ዛፍ ስር ይሄዱና ቆዳ ለበስ የሆነይ ራድዬናቸውን ከፍተው ምሳ ሰአት እስቲደርስ ጣብያ እየቀያየሩ የባጥ የቆጡን ቲሰሙ ይቆያሉ።
ምሳ በልተው ትንሽ እረፍት ይወስዱና ግቢ ውስጥ እየተንጎራደዱ እሚሰራ ስራ ቢያጡንኳ ምንም ያልሆነውን የግቢውን የንጨት አጥር ቲያጠባብቁ ይውላሉ።
የኛን የትዳር አጥር እያፈረሱ ምንም ያልሆነው የግቢያችንን አጥር ቲያጠባብቁ ታይ "እኝህ ሰው ግን ተቀልባቸው ጋር ታይጣሉም አይቀሩ!" እላለሁ።
በበሩ ፍንጭት መኖራቸውን ታረጋገጥሁ ቡሀላ ወድያው ወደ መኝታዬ ተመለስሁና እኔና ውብዬ ባቀድነው መሰረት እንዳመመው ሰው ማቃሰት ጀመርሁ።
"እህህህም •••እህህህም •••እትትትትት እህህህም•••" ለደቂቃዎይ እንዳቃሰትሁ እሳቸው ሰምተው ምንሆንክም ታይሉኝ እኔ ደከመይ ።
ዦሮዎትም አይስማ እንዴ የተዋቡ አባት አልሁና ትንሽ አረፌ ፣ ትንፋሽ ወስጄ ድምጤን ዘለግ አድርጌ ማቃሰቴን ቀጠልሁ ••• ።
ምንም ታይሉዪ ቆይተው ተዋቡ እምኝታ ቤቷ ሆኖ ሰምታዪ ነው መሰለዪ (መቸስ መስማቷ አይቀርም)
"ባሌ ምጥ ላይ እንዳለይ ሴት እሄን ሁሉ ቲያቃስት አባዬ ምንሆንክ የማይለው አልሰማሁም ለማለት ነው? " ብላ ነው መሰል ተትልቁ ቤት ብቅ ትትል እሳቸውም የሷን መውጣት ጠብቀው•••
"ተዋቡ እሄ ልዥ በደናው ነው?" ብለው ቲጠይቋት ትለሰማሁ ማቃሰቴን ገታ አድርጌ ምላሿን መጠበቅ ዠመርሁ።
እንዳልሰማይ ስትሆን ደግመው ጠየቋት።
" ማነው እሱ ?" አለይ እንዳላወቀይ መስላ።
"ያንቺው አንዳርጌ ነዋ !" አሉ የተዋቡ አባት አያ ዘርጋው።
ጉድ እኮ ነው እናንተ የሷ መሆኔን ታወቁ ዛድያ የሷን ነገር ለኔው ትተውልይ ብሄዱ ምናለ ያንቺው እያሉ ተሷ መነጠል ምን ይሉታል? ።
ባልና ሚሽት ማራራቅ ለትዳር ይጠቅማል የሚል ጥሁፍ ተይትኛው መጥሀፍ ላይ ነው ያነበቡት? እያልሁ በልቤ የኔዋ ተዋቡ•••
"ኧረ እንጃ ! ምን ሆኗል ? መችስ ተነሳ? ምን ሰማህ አቡዋ!?" ትትል ሰማሁ ። አይ ተዋቡ ያልተስተማረይ ምሁር ነይ እኮ እምዋን ይንሳይ።
"እኔ ምን አውቃለሁ ? እየቃዥ ይሁን አሞት ብቻ ሲያቃስት የሰማሁ መሰለዪ" አሏት።
"መች አሁን ነው?" አለይ ተዋቡ።
ኧረ እዚህ ተተቀመጥሁ ዥምሮ እያቃሰተ ነው በጤናውም አይመስለይ!"አሉ።
ጆሮዬን ማመን ተሳነይ ዛድያ ተተቀመጡ ጀምሮ እየሰሙዪ ኖሯል እንደዛ ትንፋሽ እስቲያጥረይዪ ታቃስት ዝም ያሉይ !! እኔስ በጤናዬ ነው እርሶ ግን ጤነኛም አይመስሉዪ አልሁ ባይሰሙኝም ንዴቴን ልትንፍሰው ብዬ።
"እስቲ ቆይ" አለችና ወደ በሬ ተጠግታ አንኳኳይ።
ቲያቀብጠኝ እንዴ ትድገመው ብዬ ዝም ስል•••
ክፍል - አምስት [፭]
.
.
.
በዚህ መሀል እኔና ሚሽቴ ካለንበትን ክፍል አባቷ ወደ ተኙበት ክፍል የሚያስገባው መሀለኛው በር የተንጠለጠለው መጋረጃ ገለጥ ሲል እኔም የኔ ተዋቡም እኩል አየነው ድምጣችን ብቻ ታይሆን ትንፋሻችን ጠፋ••••••
የተገለጠው መጋረጇ ወደ ቦታው ቲመለስ አይተውን ተመልሰው ሄደው ተኙ እንዴ? ብዬ ጆሮዬን ትቀስር ማንኮራፋታቸው ድምጡ ቢቀንስም አሁንም ጨርሶ አልጠፋም።
እያንኮራፉ ነው ።እሳቸው ተሆኑ መጋረጃውን የገለጡት ምንግዜ ተኝተው ምንግዜ ማንኮራፋታቸውን ቀጠሉ እያልሁ በመሀል ወደ ክፋሉ ወለል ትመለከት መጋረጃውን እንደሰው ገልጦ የገባው
ያ ጥላሸት የመሰለ የተዋቡ ድመት ሽቅብ እያየዪ ይንጠራራል።
ደንግጣ ወደ እምትቁለጨለጨው ተዋቡ ጆሮ ጠጋ አልሁን
"ኤድያ ቆሌውን ይግፈፈውና ያ ሻንቅላ ድመትሽ ነው ባክሽ ቄሌያችንን የገፈፈው እሄው እታች ቆሞ እየገላመጠኝ ይንጠራራል ፣ እኔማ አንዳንዴ አስተያየቱን ስመለከት እንደማልወደው ልቡ የነገረው እኮ ነው የሚመስለኝ ።
መጥቶ አጠገብሽ ሊተኛ አስቧል መሰል ሄዶ ላባትሽ ተማቃጠሩ በፊት ቦታ ልልቀቅለት "
ብያት በገዛ ቤቷ እንደልቧ የመሳቅ መብቷን የተነጠቀይው ተዋቡ ታፈናት ሳቅ ጋር ትትታገል እኔ ተነስቼ በገባሁባት መስኮት ወደ ክፍሌ ተመለስሁ።
መስኮቷን ስዘጋት ቅድም ትከፍታት ተጮኸችው በላይ
"ቀርርርርርርር እያለይ ትትጮህ ተሳቀኹይ ኧረ እሚያሳቅቅ ነገር ያሳቆት አቦ
ተዋቡ አቅሏን ስታ ስትጬህ አፏን አፈንኋት ይችን መስኮት ምኗን ላፍናት እናንተው?"
ጥርሴን መንከሴ ተጩኸት ያስጥላት ይመስል ጥርሴን ነክሼ ዘጋኋትና "ነግቶ ተዋቡ ትትነሳ ተውስጥ ትሸጉረዋለይ " እያልሁ ታጣፊዋ አልጋዬን ቁልቁል ታያት አስጠላችኝ።
በላብ ተሚያጠምቅ የፍቅር እሳት ተሚዘንብበት አልጋ ላይ አውርደህ በረዶ ላይ ያስተኛኸይ የተዋቡ አባት የስራህን ይስጥህ ብዬ ሽቅብ ተራገምሁና ተጠቅልዬ ተኛሁ።
ተሁለት ቀን ቡሀላ ዳግም መስኮቷን ከፈተችልይ። ተመግባቴ በፊት
"አባቷ ሰማ አልሰማ እያልሁ ታልሳቀቅ አልጋውንም ተዋቡንም እያስጮሁክ ታሰኛይ እኔም እየጮሁክ የልቤን በማድረስ አባቷ በብስጭት በውድቅት ለሊት በሮ እንዲጠፋ ታላረግሁ እኔ አንዳርጌ አይደለሁም !!"
ብዬ ፈክሬ ገባሁ። ተገባሁ ኋላ ግን ተዋቡ "ተው ቀስበል አለሜ አብዋ እንዳይሰማ !"
እያለይ ስለምነይ ለሷ ትል ተውሁት። አቧቷ በመሀል ድንገት ማንኮሯፋቱን አቁሞ መገላበጥ ቲያበዛ ተዋቡ •••
"ታይሰማን አይቀርም!" ብላ በጭንቀት ነፍሷ ልትወጣ ደረሰይ። እኔም የሷ ጭንቀት ትላስጨነቀይ በመሀል አቋርጬ ድምጣችንን አጥፍተን ትንሽ ቆየንና መገላበጡን አቁሞ ማንኮራፋት ቲጀምር ተነስቼ ወደክፍሌ ተመለስሁ።
ተስድስት ቀን በላይ በግዜ እየገባሁ እክፍሌ እያመሸው ብቆይም አባቷ ሀሳባቸውን ለመቀየር ፍንጭም ታያሳዩ ስለቆዩ ተበሳጨሁ።
እኝህ ሰው በምን ብልሀት ተኔም ተሚሽቴም አናት ላይ ሊወርዱ እንደሚችሉ ቁጭ ብዬ ታሰላስል ዋልሁ። አንድ ሀሳብ ስለመጣልይ ተዋቡ ማታ እራት ይዛ ክፍሌ ትትመጣ ያሰብሁትን ነገርዃት።
ምን አሰብሁ መሰለሽ ውብ አለሜ እኔ ሆን ብዬ ታምሚያለሁ ብዬ እተኛለሁ ። ያኔ አንቺ እንደተጨነቅሽ ሆነሽ •••
"እንዲህ ታሞማ ብቻውን እይህ ክፍል ውስጥ መተኛቱ ደግ አደለም እላይ ቤት ተኝቶ ላስታመው እይ ብለሽ ሀሳብ ታቀርቢያለሽ ።
መቼስ ሰው ናቸውና ታምሜ እያዩ አይሆንም አይሉም አደል?" ስላት።
"ኧረ አይልም አባዬ እኮ እንደሀይለኝነቱ ሁሉ ሩህሩህ ነው !" አለይ።
"ደግ እንግዲህ አንዴ እላይ ቤት ተገባሁ ቡሀላ ተሻለኝም አልተሻለኝም እይህ የሚቀመጡበት ምህንያት ስለማይኖራቸው መሄዳቸው አይቀርም"
"ልክ ብለሀል! አወይ አለሜ እንደው ምን ስትል እሄን መላ አሰብኸው በል !
ታብዋ ጋር ታንቀያየም በሰላም ችግራችንን የምንፈታበት ብልህ መላ ነው።
በል ነገ ተምኝታህም ሳትነሳ የታመምህ መስለህ ተኛ!" ብላይ ወጣይ።
አባቷ ጥዋት ጥዋት እኔ ታለሁባት ክፍል በር ላይ ጠሀይ እንደሚሞቁ አውቃለሁ ። ተንቅልፌ ቀደም ብዬ ብነቃም ሰአታቸው እስክትደርስ እዛው ትገላበጥ ቆየሁ።
ሁለት ሰአት ላይ ተምኝታዬ ተነስቼ በበሩ ፍንጭት ወደ ውጪ አጮለቅሁ።
እተለመደው ቦታ በርጬማቸው ላይ ተቀምጠው ጠሀይ እየሞቁ ዳዊት ቲደግሙ አየኋቸው••••
"ተሀምሳ ዳዊት የልብ ቅንነት" አለይ እምዋ
የኛን ትዳር እያሳመሙ ዳዊት ቢደግሙ ምን ዋጋ አለው።
ለሊቱን አብረን እንዳንሆን መከልከላቸው ታያንስ ቀንም እንደወንድ ወጣ ብለው ስለማይመለሱ እምንገናኝበትን ቀዳዳ ሁሉ ደፍነው በናፍቆት ርሀብ እየቀጡን ዳዊት ትለደገሙ ተቅጣት የሚያመልጡ መሰላቸው እንዴ?
ተመጡ ጀምሮ የለሊቱ ይሁን ቀን እንኳን ተቤት አይወጡም እኮ እናንተው
ተሁለት እስተ አራት ሰአት ጠሀይ ቲሞቁ ይቆያሉ ።
ጠሀይዋ አየል እያለይ ትትመጣ ተነስተው ግቢ ውስጥ ወዳለ አንድ ትልቅ ዛፍ ስር ይሄዱና ቆዳ ለበስ የሆነይ ራድዬናቸውን ከፍተው ምሳ ሰአት እስቲደርስ ጣብያ እየቀያየሩ የባጥ የቆጡን ቲሰሙ ይቆያሉ።
ምሳ በልተው ትንሽ እረፍት ይወስዱና ግቢ ውስጥ እየተንጎራደዱ እሚሰራ ስራ ቢያጡንኳ ምንም ያልሆነውን የግቢውን የንጨት አጥር ቲያጠባብቁ ይውላሉ።
የኛን የትዳር አጥር እያፈረሱ ምንም ያልሆነው የግቢያችንን አጥር ቲያጠባብቁ ታይ "እኝህ ሰው ግን ተቀልባቸው ጋር ታይጣሉም አይቀሩ!" እላለሁ።
በበሩ ፍንጭት መኖራቸውን ታረጋገጥሁ ቡሀላ ወድያው ወደ መኝታዬ ተመለስሁና እኔና ውብዬ ባቀድነው መሰረት እንዳመመው ሰው ማቃሰት ጀመርሁ።
"እህህህም •••እህህህም •••እትትትትት እህህህም•••" ለደቂቃዎይ እንዳቃሰትሁ እሳቸው ሰምተው ምንሆንክም ታይሉኝ እኔ ደከመይ ።
ዦሮዎትም አይስማ እንዴ የተዋቡ አባት አልሁና ትንሽ አረፌ ፣ ትንፋሽ ወስጄ ድምጤን ዘለግ አድርጌ ማቃሰቴን ቀጠልሁ ••• ።
ምንም ታይሉዪ ቆይተው ተዋቡ እምኝታ ቤቷ ሆኖ ሰምታዪ ነው መሰለዪ (መቸስ መስማቷ አይቀርም)
"ባሌ ምጥ ላይ እንዳለይ ሴት እሄን ሁሉ ቲያቃስት አባዬ ምንሆንክ የማይለው አልሰማሁም ለማለት ነው? " ብላ ነው መሰል ተትልቁ ቤት ብቅ ትትል እሳቸውም የሷን መውጣት ጠብቀው•••
"ተዋቡ እሄ ልዥ በደናው ነው?" ብለው ቲጠይቋት ትለሰማሁ ማቃሰቴን ገታ አድርጌ ምላሿን መጠበቅ ዠመርሁ።
እንዳልሰማይ ስትሆን ደግመው ጠየቋት።
" ማነው እሱ ?" አለይ እንዳላወቀይ መስላ።
"ያንቺው አንዳርጌ ነዋ !" አሉ የተዋቡ አባት አያ ዘርጋው።
ጉድ እኮ ነው እናንተ የሷ መሆኔን ታወቁ ዛድያ የሷን ነገር ለኔው ትተውልይ ብሄዱ ምናለ ያንቺው እያሉ ተሷ መነጠል ምን ይሉታል? ።
ባልና ሚሽት ማራራቅ ለትዳር ይጠቅማል የሚል ጥሁፍ ተይትኛው መጥሀፍ ላይ ነው ያነበቡት? እያልሁ በልቤ የኔዋ ተዋቡ•••
"ኧረ እንጃ ! ምን ሆኗል ? መችስ ተነሳ? ምን ሰማህ አቡዋ!?" ትትል ሰማሁ ። አይ ተዋቡ ያልተስተማረይ ምሁር ነይ እኮ እምዋን ይንሳይ።
"እኔ ምን አውቃለሁ ? እየቃዥ ይሁን አሞት ብቻ ሲያቃስት የሰማሁ መሰለዪ" አሏት።
"መች አሁን ነው?" አለይ ተዋቡ።
ኧረ እዚህ ተተቀመጥሁ ዥምሮ እያቃሰተ ነው በጤናውም አይመስለይ!"አሉ።
ጆሮዬን ማመን ተሳነይ ዛድያ ተተቀመጡ ጀምሮ እየሰሙዪ ኖሯል እንደዛ ትንፋሽ እስቲያጥረይዪ ታቃስት ዝም ያሉይ !! እኔስ በጤናዬ ነው እርሶ ግን ጤነኛም አይመስሉዪ አልሁ ባይሰሙኝም ንዴቴን ልትንፍሰው ብዬ።
"እስቲ ቆይ" አለችና ወደ በሬ ተጠግታ አንኳኳይ።
ቲያቀብጠኝ እንዴ ትድገመው ብዬ ዝም ስል•••