👩◈ ሚስቴና አባቷ ◈👴🏻
ክፍል - ስድስት [፮]
✍ (በጥላሁን ተስፋዬ)
.
.
.
....ምን አቀበጠይ።
"ሳልታመም ታምሚያለሁ ብዬ የእውነት አደረከው ኧረ ይቅር በለኝ ጌታዬ !"••••
ሚሽቴምኮ አብራይ ተሰቃየይ ነገሩ አብረን ነን እሄን ተንኮል የሸረብነው ቢሆንም ማስታመም ተመታመም አይተናነስምና ለሷ ጭንቀት ስትል ማረይ!! " አልሁ ተልቤ።ጭንቁ ቲበዛብይ።
ተምሽቱ አንድ ሰአት አከባቢ የገባሁ ሁሉ ወጥቶ አለቀ መሰለይ ሁሉም ነገር ቀጥ አለ። ተሶስት ሰአት በላይ በተከታታይ ቲያሯሩጠኝ ስለቆየ ሁለ መናዬ ዝሎ እራሴን ስቼ እዛቹ ታጣፊ አልጋዬ ላይ እንደተዘረጋጋሁ እንቅልፍ ጣለይ።
ምን ያህል እንደተኛሁ እንጃ ብቻ ብንን ትል ተዋቡና አቧቷ እክፍሌ ውስጥ ተቀምጠዋል።
"ነቅቷል መሰለይ ወደላይ ቤት ይዘነው እንሂድ አደል አቡዋ?" አለች የኔ ተዋቡ።
ወባ ነች ያመመችው አልሁሽ እኮ ለኔና ላንቺስ ግድ የለም ለህጣና ልጅ አታስቢም ይልቅ ሂጂና እምኝታችሁ ላይ አጎበሩን ዘርጊና ተልጅሽ ጋር ተኚ ! ዛሬን እዚሁ ይደርና እስከጥዋት ለውጥ ከሌለው ከተማ ወዳለው ሀኪም ቤት ይዘነው እንሄዳለን። አሏት።
ውባ አለሜ እባቷ እንዲያ ሲሏት በሀፍረት ኩምሽሽ ብላ አይን አይኔን ትታየኝ አየኋት።
በንዴት እርርርርርይ ብዬ ልጬህ ምንም አልቀረይ።
ልጩህ ብልስ መድሀኒት ነው ብለው ያጠጡይ በሽታ አቅም አሳጥቶኛል በምን አቅሜ እጮሀለሁ።
"ወባ ነይ ብለህ ነው አቡዋ እኔ አይመስለኝም " አለይ ኮስተር ብላ።
እቅዳችን ትላልተሳካ እና እንዳለችው ይዛኝ ወደላይቤት እንዳንገባ የማይነቀል እንቅፋት በሆኑባት በገዛ አባቷ ተማፈሯም በላይ ተናደለይ።
"ወባ ነች አንቺ ነሽ እምውቂው እኔ ይልቅ ሂጂ ልጅሽም ተነስታለይ መሰለይ ድምጣ ይሰማል?" አሏት። እሄን ግዜ ብሽቅ አልሁና •••
"ወባማ አይደለም ያመመኝ!"አልሁ።
"እና እምትንቀጠቀጠው ጎጃምኛ እየጨፈርህ ኖሯል ምን ይላል እሄ!" አሉ አባቷ በቁጣ።
"ኧረ አልተንቀጠቀጥሁም መች ተንቀጠቀጥሁ!"
እንኳን አካልህ ድምጥህም እየተንቀጠቀጠ ነው ተወባ ውጪ እንዲህ የሚያደርግ በሽታ የታለ አንተ ልዥ ሰው የሚልህን ስማ!" አሉይ አይናቸውን አፍጠው"
ዝም አልኋቸው ። ሁለቱም ዝም ብለው ቲያዩኝ እሳቸውን ትቼ ወደምሽቴ ዞርሁና
"እንደኔ እንደኔ ተሆነ ግን
ያመመኝ ወባ ታይሆን ብርድ ነው ተዋቡ።
የዚህን ክፍል ግርግዳ እይው እስቲ ተሰነጣጥቋል እኮ!!!
ያን ግዜ እሄን ቤት ጭቃ ትናስመርገው ሳንቲም ቀነሰልን ብለን በማይረባ ሰው ነው ያስመረግነው።
ምርጉ አይረባ ልስኑ አይረባ ሞላ ግርግዳው እኮ ሽንቁር ብቻ ነው ።
ብርድ የማይገባበት ቀዳዳ የለም ስልሽ እግሬን ትሸፍን ታናቴ በኩል ይገባል፣ አናቴን ትሸፈን ተጎኔ በኩል ይገባል እሱ ነው በየቅጣጫው ትነፍስብይ ሰንብቶ ለበሽታ የዳረገይ!" አልሁ።
"ዛድያ አንተ ምን ቆራጣ ብርድልብስ የለበስህ ይመስል አንዴ እግርህን አንዴ አናትህን እያልህ በፈረቃ አሸፋፈነህ? ሁለመናህን ተሸፋፍነህ ለጥ አትልም አሉኝ አቶ ዘርጋው ።የተዋቡ አባት።
ኡፍፍፍፍ ሚሽቴን ባወራትም መልስ የሚሰጡይ እሳቸው ናቸው ። አሁንስ አበዙት እኝህ ሰው ብዬ በውስጤ ተልጌልጉሜ ታልጨርስ ቀጠል አረጉና•••
"ምርጉም ሆነ ልስኑ ሽግር ታለበት ደግሞ ተሽሎህ ስትነሳ እይሁ ግቢ ውስጥ እዛ እመውጫው በር በስተግራ በኩል ትቆፍርና ድንጋዩንም ጠጠሩም ለይተህ ለምርግ የሚበቃ አፈር ታዘገጀህ ቡሀላ ጭቃ ታቦካለህ።
በየሶስት ቀኑ እያሸህ ፣እያገላበጥህ እስቲበስል ድረስ ለሁለት ሳምንት በደንብ ታቦካኸው ቡሀላ ይህን የተሰናጣጠቀ ግድግዳ አፍርሰህ ወድያ ትጥልና ግጥም አርገህ ትመርገዋለህ ! እስታሁንስ ዝም ያልከው አንተ ለዚህ አንሰህ ነው አንዳርጌ ?
ባይሆን እኔም እስተዛው እዚሁ ስላለሁ ልሱኑ ላይ አግዝሀለሁ !" ሲሉይ •••
ሀሞቴ ፍስስ አለይ።
"በለፈለፉ ባፍ ይጠፉ " ያለይው ማን ነበርሳ ። እሳቸውን ተቤቴ ላበር በጠነሰስሁር ሴራ እኔኑ ሊያበሩኝ ነው መሰል አሁንስ።
"ለማንኛቸውም እኔ ብርድ እይ ወባ አላመመኝም አላመመኝም አበቃሁ !”
አልሁና ተሸፋፍኜ ተኛሁ አባትና ልጅ ተከታትለው ተክፍሌ ወጡ ። ተውጪ ዘጉብይ።
ጥዋት ላይ ተንቅልፌ ብንን ትል ተምኝታዬ ፊት የሚሽቴ አባት ቁጭ ብለዋል።
"ደና አደርህ አንዳርጌ? አዳርህ እንዴት ነው ለውጥ አለው?"
" ምንም አልል "አልሁ እየተንጠራራሁ።
"አይዞህ ለማንኛቸውም እንዳልኸው ብርድ ተሆነ የመታህ አንድ ተቡና ጋር የምትወሰድ ፍቱን ቅጠል አለይ ታች መንደር ወርጄ ይዤልህ ልምጣ!" ሲሉይ ገና ታያመጡት አንቀጠቀጠይ።
ኧረ በዲማው ጊዬርጊስ !!!
ተሽሎኛል እኮ! እንደኔ ጤነኛ አለ እንዴ!
ብርድ•••••
ኧረ የምን ብርድ ? ለሊቱን ነው በላብ ንቅል ብሎ የወጣልይ !
አብዋ አይድከሙ፣ እውነቴን ነው ምንም የህመም ዘር ውስጤ የለም።
እንኳን ሊበርደይ ሞቆኛል!"
አልኋቸው ቅጠል ላምጣልህ ቲሉኝ በድንጋጤ ያላበኝን እግንባሬ ላይ ችፍ ያለ ላብ እየጠረግሁ።
"ታልህ ይሁን አንዳንድ በሽታ ሄድ መለስ ይላልና መልሶ ታመመህ ንገረይ !"
ብለውይ ተክፍሌ ቲወጡ አንገቴን ሽቅብና ቁልቁል እያወዛወዝሁ በጀ አልኋቸው።
እንኳን የውሸት የእውነት ብታመምስ መች ለርሶ እነግሮታለሁ ሆሆ•••ቅጠል!! አልሄድ ብላቸው እዚሁ ሊገላግሉይ አስበዋል እንዴ እኝህ ሰው።
ሳልወድ በግዳጅ በሳቸው ውሳኔ ተተሰደድኩበት ክፍል ወጥቼ በህመም ሰበብ ወደቤቴ ልመለስ ፣ ስንት አውጥቼ ስንት አውርጄይ ባመጣሁት መላ የውሸት ብታመም መዳኒት ብለው ባጠጡይ ነገር የእውነት ታምሜ ለሶስት ሰአት ያህል ሽንት ቤት ተሯሯጥሁ።
ኪሎዬም ቀነሰ፣ ወዘናዬ ተመጦ ፊቴም ገረጣ፣ አቅሜም ተዳከመ ።
ታሁን ቡሀላ እኝህ ሰው እኔና ምሽቴ ተትዳራችን መሀል ገለል ይበሉ!!! ብለን ሰላማዊ ሰልፍ ታልወጣን በስተቀር ወር ታይሞላቸው ተዛች ቤት ንቅንቅ እንደማይሉ እርግጠኛ ትለሆንኩ ተስፋ ቆረጥሁ።
አዎ እኚ ሰው በመላም በበላም አይወጡም።
ሌላ መላ ለመፈለግ መባዘኑን ይቅርብይ አልሁና የተጎዳውን አካሌን ለመጠገን ለሁለት ቀን ተክፍሌ ታልወጣ ተቀለብሁ።
ተዋቡዬም ጥሩ ጥሩውን እየሰራይ ስለምታመጣልይ በሁለት ቀን ሰውነቴም ጉልበቴም መለስ አለ።
እቤት መጠጣትም በመስኮት እንደሌባ እየገቡ ሚሽቴን ማግኘትም ምርር አለይ።
አመሻሹ ላይ ተዋቡ ታታየኝ ወጥቼ ወደ ጠጅ ቤት ሄድሁ።
ገና ገብቼ አንድ ሁለት እንዳልሁ•••
" ምን ሆነሀል ጃል? ስትገባም ሰላም አላልከኝ፣ ከገባህ ቡሀላም ሀሳብ ገብቶሀል ።
እዚህ አካልህ ተቀመጠ እይ ቀልብህ የለም እኮ በደህና ነው?" አለይ ።
ተጀርባዬ የተቀመጠው ተጠጅቤት ጋደኛቼ መሀል አንዱ የሆነው ዳምጤ።
ቀደም ብሎ ነው መሰል የገባው ሞቅ ብሎታል !
"ደህና ነይ!" አልሁት።
"አሞህ ነበር እንዴ ?ፊትህም ጭር ብሏል ሰሞኑንም መጥተህም አታውቅም ሰላም ነህ ግን ወዳጄ?" አለይ ደግሞ።
ተወኝ እስቲ ዳምጤ አልሁና ያለሁበትን ሁናታ በግርድፉ ነግሬው
"ባልና ሚስት ካንድ ወንዝ ይቀዳሉ" ይባላል የኔ ሚሽት ግን ከኔ ጋር ታይሆን ካባቷ ጋር ሳይሆን አይቀርም ካንድ ወንዝ የተቀዱት አልሁት።
ታለበት ተነስቶ ተጎኔ በመቀመጥ ለወሬ ተመቻቸና •••
"ስማ አባቷማ አባት ነው ከሱ መወለዷ ካንድ ወንዝ ከመቀዳት አይበልጥም ብለህ ነው ? ግን እሄ አባብል በመሰረቱ አይጥመኝም በጣም ነው የሚያናድደኝ !" አለይ።
"የቱ? አልሁት ።ግራ ገብቶይ።
"እሄ •••ባልና ሚሽት ታንድ ወንዝ ይቀዳሉ" የሚሉት ነገር"" አለይ።
ክፍል - ስድስት [፮]
✍ (በጥላሁን ተስፋዬ)
.
.
.
....ምን አቀበጠይ።
"ሳልታመም ታምሚያለሁ ብዬ የእውነት አደረከው ኧረ ይቅር በለኝ ጌታዬ !"••••
ሚሽቴምኮ አብራይ ተሰቃየይ ነገሩ አብረን ነን እሄን ተንኮል የሸረብነው ቢሆንም ማስታመም ተመታመም አይተናነስምና ለሷ ጭንቀት ስትል ማረይ!! " አልሁ ተልቤ።ጭንቁ ቲበዛብይ።
ተምሽቱ አንድ ሰአት አከባቢ የገባሁ ሁሉ ወጥቶ አለቀ መሰለይ ሁሉም ነገር ቀጥ አለ። ተሶስት ሰአት በላይ በተከታታይ ቲያሯሩጠኝ ስለቆየ ሁለ መናዬ ዝሎ እራሴን ስቼ እዛቹ ታጣፊ አልጋዬ ላይ እንደተዘረጋጋሁ እንቅልፍ ጣለይ።
ምን ያህል እንደተኛሁ እንጃ ብቻ ብንን ትል ተዋቡና አቧቷ እክፍሌ ውስጥ ተቀምጠዋል።
"ነቅቷል መሰለይ ወደላይ ቤት ይዘነው እንሂድ አደል አቡዋ?" አለች የኔ ተዋቡ።
ወባ ነች ያመመችው አልሁሽ እኮ ለኔና ላንቺስ ግድ የለም ለህጣና ልጅ አታስቢም ይልቅ ሂጂና እምኝታችሁ ላይ አጎበሩን ዘርጊና ተልጅሽ ጋር ተኚ ! ዛሬን እዚሁ ይደርና እስከጥዋት ለውጥ ከሌለው ከተማ ወዳለው ሀኪም ቤት ይዘነው እንሄዳለን። አሏት።
ውባ አለሜ እባቷ እንዲያ ሲሏት በሀፍረት ኩምሽሽ ብላ አይን አይኔን ትታየኝ አየኋት።
በንዴት እርርርርርይ ብዬ ልጬህ ምንም አልቀረይ።
ልጩህ ብልስ መድሀኒት ነው ብለው ያጠጡይ በሽታ አቅም አሳጥቶኛል በምን አቅሜ እጮሀለሁ።
"ወባ ነይ ብለህ ነው አቡዋ እኔ አይመስለኝም " አለይ ኮስተር ብላ።
እቅዳችን ትላልተሳካ እና እንዳለችው ይዛኝ ወደላይቤት እንዳንገባ የማይነቀል እንቅፋት በሆኑባት በገዛ አባቷ ተማፈሯም በላይ ተናደለይ።
"ወባ ነች አንቺ ነሽ እምውቂው እኔ ይልቅ ሂጂ ልጅሽም ተነስታለይ መሰለይ ድምጣ ይሰማል?" አሏት። እሄን ግዜ ብሽቅ አልሁና •••
"ወባማ አይደለም ያመመኝ!"አልሁ።
"እና እምትንቀጠቀጠው ጎጃምኛ እየጨፈርህ ኖሯል ምን ይላል እሄ!" አሉ አባቷ በቁጣ።
"ኧረ አልተንቀጠቀጥሁም መች ተንቀጠቀጥሁ!"
እንኳን አካልህ ድምጥህም እየተንቀጠቀጠ ነው ተወባ ውጪ እንዲህ የሚያደርግ በሽታ የታለ አንተ ልዥ ሰው የሚልህን ስማ!" አሉይ አይናቸውን አፍጠው"
ዝም አልኋቸው ። ሁለቱም ዝም ብለው ቲያዩኝ እሳቸውን ትቼ ወደምሽቴ ዞርሁና
"እንደኔ እንደኔ ተሆነ ግን
ያመመኝ ወባ ታይሆን ብርድ ነው ተዋቡ።
የዚህን ክፍል ግርግዳ እይው እስቲ ተሰነጣጥቋል እኮ!!!
ያን ግዜ እሄን ቤት ጭቃ ትናስመርገው ሳንቲም ቀነሰልን ብለን በማይረባ ሰው ነው ያስመረግነው።
ምርጉ አይረባ ልስኑ አይረባ ሞላ ግርግዳው እኮ ሽንቁር ብቻ ነው ።
ብርድ የማይገባበት ቀዳዳ የለም ስልሽ እግሬን ትሸፍን ታናቴ በኩል ይገባል፣ አናቴን ትሸፈን ተጎኔ በኩል ይገባል እሱ ነው በየቅጣጫው ትነፍስብይ ሰንብቶ ለበሽታ የዳረገይ!" አልሁ።
"ዛድያ አንተ ምን ቆራጣ ብርድልብስ የለበስህ ይመስል አንዴ እግርህን አንዴ አናትህን እያልህ በፈረቃ አሸፋፈነህ? ሁለመናህን ተሸፋፍነህ ለጥ አትልም አሉኝ አቶ ዘርጋው ።የተዋቡ አባት።
ኡፍፍፍፍ ሚሽቴን ባወራትም መልስ የሚሰጡይ እሳቸው ናቸው ። አሁንስ አበዙት እኝህ ሰው ብዬ በውስጤ ተልጌልጉሜ ታልጨርስ ቀጠል አረጉና•••
"ምርጉም ሆነ ልስኑ ሽግር ታለበት ደግሞ ተሽሎህ ስትነሳ እይሁ ግቢ ውስጥ እዛ እመውጫው በር በስተግራ በኩል ትቆፍርና ድንጋዩንም ጠጠሩም ለይተህ ለምርግ የሚበቃ አፈር ታዘገጀህ ቡሀላ ጭቃ ታቦካለህ።
በየሶስት ቀኑ እያሸህ ፣እያገላበጥህ እስቲበስል ድረስ ለሁለት ሳምንት በደንብ ታቦካኸው ቡሀላ ይህን የተሰናጣጠቀ ግድግዳ አፍርሰህ ወድያ ትጥልና ግጥም አርገህ ትመርገዋለህ ! እስታሁንስ ዝም ያልከው አንተ ለዚህ አንሰህ ነው አንዳርጌ ?
ባይሆን እኔም እስተዛው እዚሁ ስላለሁ ልሱኑ ላይ አግዝሀለሁ !" ሲሉይ •••
ሀሞቴ ፍስስ አለይ።
"በለፈለፉ ባፍ ይጠፉ " ያለይው ማን ነበርሳ ። እሳቸውን ተቤቴ ላበር በጠነሰስሁር ሴራ እኔኑ ሊያበሩኝ ነው መሰል አሁንስ።
"ለማንኛቸውም እኔ ብርድ እይ ወባ አላመመኝም አላመመኝም አበቃሁ !”
አልሁና ተሸፋፍኜ ተኛሁ አባትና ልጅ ተከታትለው ተክፍሌ ወጡ ። ተውጪ ዘጉብይ።
ጥዋት ላይ ተንቅልፌ ብንን ትል ተምኝታዬ ፊት የሚሽቴ አባት ቁጭ ብለዋል።
"ደና አደርህ አንዳርጌ? አዳርህ እንዴት ነው ለውጥ አለው?"
" ምንም አልል "አልሁ እየተንጠራራሁ።
"አይዞህ ለማንኛቸውም እንዳልኸው ብርድ ተሆነ የመታህ አንድ ተቡና ጋር የምትወሰድ ፍቱን ቅጠል አለይ ታች መንደር ወርጄ ይዤልህ ልምጣ!" ሲሉይ ገና ታያመጡት አንቀጠቀጠይ።
ኧረ በዲማው ጊዬርጊስ !!!
ተሽሎኛል እኮ! እንደኔ ጤነኛ አለ እንዴ!
ብርድ•••••
ኧረ የምን ብርድ ? ለሊቱን ነው በላብ ንቅል ብሎ የወጣልይ !
አብዋ አይድከሙ፣ እውነቴን ነው ምንም የህመም ዘር ውስጤ የለም።
እንኳን ሊበርደይ ሞቆኛል!"
አልኋቸው ቅጠል ላምጣልህ ቲሉኝ በድንጋጤ ያላበኝን እግንባሬ ላይ ችፍ ያለ ላብ እየጠረግሁ።
"ታልህ ይሁን አንዳንድ በሽታ ሄድ መለስ ይላልና መልሶ ታመመህ ንገረይ !"
ብለውይ ተክፍሌ ቲወጡ አንገቴን ሽቅብና ቁልቁል እያወዛወዝሁ በጀ አልኋቸው።
እንኳን የውሸት የእውነት ብታመምስ መች ለርሶ እነግሮታለሁ ሆሆ•••ቅጠል!! አልሄድ ብላቸው እዚሁ ሊገላግሉይ አስበዋል እንዴ እኝህ ሰው።
ሳልወድ በግዳጅ በሳቸው ውሳኔ ተተሰደድኩበት ክፍል ወጥቼ በህመም ሰበብ ወደቤቴ ልመለስ ፣ ስንት አውጥቼ ስንት አውርጄይ ባመጣሁት መላ የውሸት ብታመም መዳኒት ብለው ባጠጡይ ነገር የእውነት ታምሜ ለሶስት ሰአት ያህል ሽንት ቤት ተሯሯጥሁ።
ኪሎዬም ቀነሰ፣ ወዘናዬ ተመጦ ፊቴም ገረጣ፣ አቅሜም ተዳከመ ።
ታሁን ቡሀላ እኝህ ሰው እኔና ምሽቴ ተትዳራችን መሀል ገለል ይበሉ!!! ብለን ሰላማዊ ሰልፍ ታልወጣን በስተቀር ወር ታይሞላቸው ተዛች ቤት ንቅንቅ እንደማይሉ እርግጠኛ ትለሆንኩ ተስፋ ቆረጥሁ።
አዎ እኚ ሰው በመላም በበላም አይወጡም።
ሌላ መላ ለመፈለግ መባዘኑን ይቅርብይ አልሁና የተጎዳውን አካሌን ለመጠገን ለሁለት ቀን ተክፍሌ ታልወጣ ተቀለብሁ።
ተዋቡዬም ጥሩ ጥሩውን እየሰራይ ስለምታመጣልይ በሁለት ቀን ሰውነቴም ጉልበቴም መለስ አለ።
እቤት መጠጣትም በመስኮት እንደሌባ እየገቡ ሚሽቴን ማግኘትም ምርር አለይ።
አመሻሹ ላይ ተዋቡ ታታየኝ ወጥቼ ወደ ጠጅ ቤት ሄድሁ።
ገና ገብቼ አንድ ሁለት እንዳልሁ•••
" ምን ሆነሀል ጃል? ስትገባም ሰላም አላልከኝ፣ ከገባህ ቡሀላም ሀሳብ ገብቶሀል ።
እዚህ አካልህ ተቀመጠ እይ ቀልብህ የለም እኮ በደህና ነው?" አለይ ።
ተጀርባዬ የተቀመጠው ተጠጅቤት ጋደኛቼ መሀል አንዱ የሆነው ዳምጤ።
ቀደም ብሎ ነው መሰል የገባው ሞቅ ብሎታል !
"ደህና ነይ!" አልሁት።
"አሞህ ነበር እንዴ ?ፊትህም ጭር ብሏል ሰሞኑንም መጥተህም አታውቅም ሰላም ነህ ግን ወዳጄ?" አለይ ደግሞ።
ተወኝ እስቲ ዳምጤ አልሁና ያለሁበትን ሁናታ በግርድፉ ነግሬው
"ባልና ሚስት ካንድ ወንዝ ይቀዳሉ" ይባላል የኔ ሚሽት ግን ከኔ ጋር ታይሆን ካባቷ ጋር ሳይሆን አይቀርም ካንድ ወንዝ የተቀዱት አልሁት።
ታለበት ተነስቶ ተጎኔ በመቀመጥ ለወሬ ተመቻቸና •••
"ስማ አባቷማ አባት ነው ከሱ መወለዷ ካንድ ወንዝ ከመቀዳት አይበልጥም ብለህ ነው ? ግን እሄ አባብል በመሰረቱ አይጥመኝም በጣም ነው የሚያናድደኝ !" አለይ።
"የቱ? አልሁት ።ግራ ገብቶይ።
"እሄ •••ባልና ሚሽት ታንድ ወንዝ ይቀዳሉ" የሚሉት ነገር"" አለይ።