GENIUS ACADEMY


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Telegram


https://youtube.com/@geniusacademy405?si=yoKA-4qDL_tFzmIF
በዚህ ቻናል ምን ምን ያገኛሉ 🔽
➽ Textbook ( 9-12 )
➽ Teachers Guide (9-12)
➽ Textbook  (1-8)
➽ Teachers Guide (1-8)
➽ Freshman courses
➽እንዲሁም ትምህርታዊ መረጃዎችን እና ምክሮችን
✅አስተያየትዎን እዚህ 👉 @Desutech_bot ይጻፋልን❗️

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Telegram
Статистика
Фильтр публикаций


*የብሔራዊ መታወቂያ (ፍይዳ) ምዝገባን ይመለከታል*

ትምህርት ሚኒስቴ ከሰኔ 2017 ጀምሮ የዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና ለሚወስዱ ዕጩ ተመራቂዎች እና ዳግም ተፈታኞች ፈተናውን ለመውሰድ የፋይዳ መታወቂያ እንደቅድመ ሁኔታ መቀመጡ ይታወቃል። በመሆኑም በተቋማችሁ እየተማሩ ያሉና ከዚህ ቀደም ተፈትነው ማለፊያ ውጤት ሳያሟሉ የቀሩ የተቋማችሁ ተፈታኞች ከወዲሁ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ምዝገባ እንዲያካሂዱ ባሉት አማራጮች በሙሉ በቂ መረጃ እንድታደርሷቸው እናሳስባለን።

*ማሳሰቢያ፡*
1.ለመጀመሪያ ዙር ተፈታኞች መረጃ ማስገቢያ ሲስተም (https://eap.ethernet.edu.et )  ላይ ማስተካካያ ስልተደረገ በቅርቡ ORIENTATION የምንሰጥ ይሆናል።
2.ዳግም ተፈታኝ አመልካቾች ከሚያዝያ 14/2017 ዓ.ም -- ግንቦት 05/2017 ዓ.ም ድረስ  ከላይ የተጠቀሱትን ቅድመ ሁኔታዎች በማሟላት በ  https://exam.ethernet.edu.et በኩል መመዝገብ ይችላሉ።
3.ዳግም ተፈታኞች የአገልግሎት ክፍያ የሚከፍሉት በቴሌ ብር በኩል ብቻ ነው።

የኢፌድሪ ትምህርት ሚኒስቴር


“እንደተናገረ ተነስቷል” ማቴ 28፡6

እንኳን ለጌታችንና ለመድኅኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ መታሰብያ በአል አደረሰን አደረሳችሁ።

በአሉን የሰላም  የፍቅር የደስታ ያድርግልን።

መልካም የፋሲካ በአል 🐏🐏🐏
H A P P Y| E A S T E R

#GeniusAcademy
@genius_acadamy
@genius_acadamy


ከላይኛው የቀጠለ...

በዚህም የመምህርነት ሞያውን በደብረዘይት ከተማ "BCI Academy " ከዛሬ ስድስት ዓመት በፊት በፊዚክስ አስተማሪነት ይጀምራል።

ለ3 ዓመታት በመምህርነት ተቀጥሮ ከሰራ በኋላም በቢሾፍቱ ከተማ "School of My Seed" የሚባል የማጠናከሪያ ትምህርት መስጫ ተቋም አቋቁሞ የፊዚክስ የትምህርትን እያስተማረ በማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ ቪዲዮችን መልቀቅ ጀመረ።

በተለያዩ የማኅበራዊ ገፆች ላይ ያሉት አብዛኞቹ ቪዲዮዎቹ የሚቀረጹት በማጠናከሪያ የትምህርት ፕሮግራም ላይ ሳለ የቀረጻቸው መሆኑን የሚናገረው መምህር ዳኛቸው የዚህን ያህል ተቀባይነት ይኖረዋል ብሎ እንዳላሰበ ይናገራል።

የማጠናከሪያ ትምህርት ተቋሙን ከባለቤቱ ጋር በመመካከርጀመረው 16 ተማሪዎችን በመያዝ ነበረ። ከጊዜ ወደ ጊዜ ግን የተማሪዎች ቁጥር እየጨመረ ሌሎች መምህራንንም ቀጥረው ማስተማር ቀጠሉ።

በቢሾፍቱ ከተማ ለመጀመሪያ ጊዜ በነፃ 24 ሰዓት የሚያገለግል የተማሪዎች ቤተ-መጽሐፍ ቤት በማዘጋጀትም ማንኛውም ተማሪ በነፃ አገልግሎት እንዲያገኝ አድርጎም እንደነበር አስታውሷል።

መምህር ዳኛቸው ከ2000 በላይ የሚሆኑ ተማሪዎችን ማስተማሩን ይናገራህ። ሆኖም ይህ ጥረቱ ሳያስበው በአጭርተቀጨ። ተቋሙ ተዘግቶ ማስተማር አትችልም የሚል ትዕዛዝ ተሰጠው።

ምን ተፈጠረ ?

በዘንድሮው ዓመት 50 አካባቢ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችን ለማስተማር አቅድ ማውጣቱን፤ ነገር ግን የተመዝጋቢዎች ቁጥር ግን ከ300 መሻገሩን ይጠቅሳል።

"ሁሉንም የምናስተምርበት አቅሙ ስላልነበረን ግዴታ ተማሪዎቹን መፈተን ነበረብን እና ፈትነን መቶ ተማሪዎችን በውጤታቸው መርጠን ማስተማር ጀመርን'' ሂደቱን ያስረዳል።

ሥራቸውን ከጀመሩ በኋላ ግን ማስተማር አትችልም ተብሎ ተቋሙ እንደተዘጋበት እና በመጀመሪያ የተለያዩ ምክንያቶች ቢቀርቡለትም ኋላ ላይ ግን ነገሩ ሌላ መሆኑን እንደተረዳ ይናገራል።

መምህር ዳኛቸው ገለጻ ሳይመረጡ ከቀሩት ተማሪዎች መካከል አንዷ ተማሪ የከተማው "ከፍተኛ ባለስልጣን " ልጅ እንደነበረችና እና፣ እሷን ባለመምረጣቸው ተቋሙ እንዲዘጋ ትዕዛዝ እንደወጣበት ይናገራል።

በቻለው አቅም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ለመግባባት ቢሞክርም ሳይሳካ ቀርቶ ወደ አዲስ አበባ በመምጣት በኦንላይን ማስተማር ጀምሯል።

መምህር ዳኛቸው አሁን ላይም ከሀገር ውጭ ያሉ 16 ተማሪዎችን በኦንላይን እያስተማረ ይገኛል።

ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር በነበረው ቆይታ በቢሾፍቱ ከተማ ያቆሙትን የማስተማር ስራቸውን በአዲስአበባ ከተማ ለማስቀጠል ጥረት እያደረገ እንደሆነ ነግሮናል።

በቀጣይስ ?

"አንድ ነገር እፈልጋለሁ፣ ሰርቭ ( serve ) የማደርግበት መንገድ ቢመቻችልኝ፣ ልጆች አንድም ለእናት የለቅሶ ምክንያት፣ ለአባትም የጉስቁልና ምክንያት እንዳይሆኑ ባደርገቸው ነፍሴ ታርፋለች " ይሄን ለማድረግ ጥረት እያደረኩ ነው። የመንግስት አካላም ሆነ የግል ድርጅቶች እድሉን እንዲያመቻቹልኝ እፈልጋለሁ " በማለት ይናገራል።

ተማሪዎቹ ምን ይላሉ ?

እሱ ካስተማራቸው ተማሪዎች አሁን ላይ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ትምህርታቸውን የሚከታተሉ አሉ። ስለቀረቤታቸው ሲናገሩም ''መምህራችን የሚለው ቃል ያርቅብናል፣ ብቻ እሱ ከቤተሰብም በላይ ነው፡፡ እንደተማሪና መምህር ሳይሆን እንደ ልጅ እና አባት ነው፡፡'' ሲሉ ምስክርነት ይሰጣሉ።

የሚያስተምሩበት መንገድ በጣም ቀላል እና ግልፅ ከመሆኑ የተነሳ ሳይገባቸው ያለፉት ነገር እንደሌለ እና የሀገር አቀፍ ፈተና ጥሩ ውጤት ለማምጣታቸውም የመጀመሪያውን ድርሻ የሚወስዱት መምህር ዳኛቸው መሆኑን ይጠቅሳሉ።

አሁን ላይ በቢሾፍቱ ማስተማራቸውን እንዲያቆሙ መደረጉ መጭው ትውልድን መበደል ነው ሲሉም የቀድሞ ተማሪዎቻቸው ይናገራሉ።

@genius_acadamy
@genius_acadamy


የፊዚክስ መምህሩ ማነው ?

#Ethiopia | ከሰሞኑ በተለያዩ ማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይየፊዚክስ መምህሩ የሚያስተምሩበት መንገድ በቪዲዮ ከተለቀቀ በኋላ እንደ አዲስ በበርካቶች ዘንድ አድናቆት እየተቸረው ነው፡፡

ከሰሞኑ በበርካቶች ዘንድ መነጋገሪያ የሆነውን የፊዚክስ መምህር ቲክቫህ ኢትዮጵያ አግኝቶ ስለ ልምዱና ስለ አጠቃላይሥራው ጠይቋል።

የፊዚክስ መምህሩ ዳኛቸው ሻምበል ይባላል። ውልደት እና እድገቱ በድሬዳዋ ሲሆን እስከ 12ኛ ክፍል ትምህርቱን ያጠናቀቀው በድሬደዋ ብስራተ ገብርኤል ትምህርት ቤት ነው፡፡

በአዲስአበባ ዩኒቨርሲቲም የሜካኒካል ምህንድስና የትምህርት ክፍል ተቀላቅሎ 1 ዓመት ከ6 ወር ቢማርም በኋላ ባልሆነ ሱስ ተጠምዶ ትምህርቱን ማጠናቀቅ ሳይችል እንደቀረ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር በነበረው ቆይታ ያስታውሳል።

ወደ ቻይና የመሄድ እድል ያገኘው ዳኛቸው፥ ሀንዦ በሚባል ትምህርት ቤት በኮምፒውተር ሳይንስ ትምህርቱን ተከታትሎ በጥሩ ውጤት አጠናቆ ወደ ሀገር ቢመለስም የነበረበት ሱስ ህይወቱን እጅግ ፈታኝ አደረገበት።

በዚህ ምክንያትም ወደ ጎዳና ህይወት መግባቱን የሚናገረው መምህር ዳኛቸው፤ ኑሮውን በአዲስ አበባ ጎዳኖች ላይያደረገበት የህይወት አጋጣሚም ነበረ።

ታዲያ የመምህሩ ህይወት እንዴት ተቀየረ ?

ከቢሾፍቱ አዲስ አበባ ቅዳሜ እና እሁድ ለሥራ ስትመላለስ የነበረች ነርስ ጋር አጋጣሚ ያስተዋውቃቸውና ታሪኩን እንዳካፈላት፤ ታሪኩን ከሰማች በኋላም በማዘኗ ግንኙነታቸው እንደቀጠለ ያስረዳል።

ይህች ሴት የአሁን ባለቤቱ እንደሆነች የነገረን መምህርዳኛቸው፥ በሷ ድጋፍና እርዳታ የጎዳና ህይወቱ ማብቃቱን አጫውቶናል፡፡

ለአባቱ ልዩ ክብር እንደነበረው የሚናገረው መምህር ዳኛቸው ከጎዳና ህይወት ከወጣ በኋላ ወደ መምህርነት ለመግባቱም አባቱ ለእሱ የከፈለው ውለታ ጉልበት እንደሆነው ይናገራል።


ለመላው የእስልምና እምነት ተከታይ ቤተሰቦቻችን እንኳን ለረመዷን ፆም ፍቺ አደረሳችሁ። EID Mubarek my beloved Families🙏❤️

@genius_acadamy
@genius_acadamy


★ የመውጫ /ExitExam/ ፈተና ወስደው ለወደቁ ተማሪዎች Special Diploma ሊሰጥ ነው።

የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት ፅ/ቤት ከትምህርት ሚኒስቴር አመራሮች ጋር ተከታታይ ውይይት ሲያደርግ
ቆይቷል፡፡

የመውጫ ፈተና መሰጠት ከተጀመረበት ሐምሌ 2015 ዓ.ም ጀምሮ ፈተናውን ወስደው ለወደቁ ዕጩ ተመራቂዎች ልዩ ዲፕሎማ ሰርተፊኬት በቅርቡ መሠጠት እንዲጀመር ውሳኔ ላይ መድረሱን አሳውቋል።

ተማሪዎቹ ሥራ እየሠሩ በማንኛውም ጊዜ የመውጫ ፈተናውን በድጋሜ መውሰድ የሚችሉበት ዕድል ክፍት እንዲሆን መደረጉንም ገልጿል።

ፈተናውን ወስደው የሚያልፉ ተፈታኞች በስፔሻል ዲፕሎማው ምትክ ዲግሪ ይሰጣቸዋል ተብሏል።

የስፔሻል ዲፕሎማ የደመወዝ ስኬል እንዲወጣለት ከትምህርት ሚኒስቴር እና ከስቪል ሰርቪስ ጋር ውይይት እየተደረገ መሆኑን ህብረቱ አሳውቋል።

@genius_acadamy
@genius_acadamy


#MoE

ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተመራቂዎች የዲግሪ ሰርተፊኬት ህትመት በአንድ ማዕከል ሊከወን ነው።

የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ለሁሉም የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች እና ለሁሉም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በጻፉት ሰርኩላር "በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰጡ ዲግሪዎች ህትመት ወጥ በሆነ መልኩ ደህንነታቸው ተጠበቆ የዲግሪ ማስረጃ/ሰርተፍኬት ህትመት በማዕከል ለማሳተም መታሰቡን" ገልፀዋል።

በመሆኑም ተቋማቱ በዲግሪ የምስክር ወረቀቱ ላይ ሊካተትላችሁ የሚፈልጉትን ሎጎ እና ሌሎች መካተት አለበት የሚሉትን እንዲያካትቱ እንዲሁም በየተቋማቱ በዚህ ዓመት የመውጫ ፈተና ወስደው ያለፉና ለምርቃት የተዘጋጁ የተማሪዎች ዝርዝር እንዲልኩ ሚኒስትሩ አሳስበዋል።

የህትመት ሥራው በ2017 ዓ.ም ከሚመረቁ ተማሪዎች ጀምሮ የሚፈፀም መሆኑንም ገልፀዋል።


#Update #NGAT

የብሄራዊ ድህረ-ምረቃ (NGAT) መግቢያ ፈተና መጋቢት 5 እንደሚሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።

ትምህርት ሚኒስቴር በ2017 ዓ.ም የሶስተኛ ዙር የNGAT አመልካቾች ምዘገባ መጠናቀቁን ገልጿን።

ፈተናው የሚሰጠው ዓርብ መጋቢት 5 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ጀምሮ መሆኑንም አሳውቋል።

ተፈታኞች  በተጠቀሰው ቀንና ሰዓት በሚመደቡበት የፈተና ማዕከላት እንዲገኙ ብሏል።

➡️ ተፈታኞች ወደ ፈተና ማዕከል በሚሄዱበት ወቅት ማንነታቸውን የሚገልጽ መታወቂያ መያዝ ይጠበቅባቸዋል።

➡️ ማንኛውም ተፈታኝ ፈተናው ከመጀመሩ 3 ደቂቃ በፊት በፈተና ማዕከል መገኘት ይጠበቅበታል፡፡

➡️ የሞባይል ስልክ ይዞ በፈተና ማዕከል መገኘት ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡

➡️ የፈተና ማዕከላት ምደባ በምዝገባ ፕላትፎርም የሚገለጽ ይሆናል፡፡

#MoE


#MoE

በሰኔ 2017 ዓ.ም የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና የሚወስዱ ዕጩ ተመራቂዎች የፋይዳ መታወቂያ ሊያወጡ ይገባል። - ትምህርት ሚኒስቴር

የካቲት 21/2017 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ተፈርሞ ለሁሉም የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተላከ ሰርኩላር፤ ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተማሪ እና የሠራተኞችን መረጃ በተደራጀ መልኩ ለመያዝ ጠቀሜታ እንዳለው ይገልጻል።

የሀገር አቀፍ ፈተናዎችን ደህንነት ለማስጠበቅ አስፈላጊ መሆኑንም ያትታል።

በዚህም በሰኔ 2017 ዓ.ም የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና የሚወስዱ ዕጩ ተመራቂዎች ፈተናውን ለመውሰድ የፋይዳ መታወቂያ ሊያወጡ እንደሚገባ አሳስቧል።

@genius_acadamy
@genius_acadamy


እንኳን 129ኛው የአድዋ ድል በዓል  አደረሳችሁ!!!


የዐፄ ምኒልክ የዐድዋ ጦርነት የክትት አዋጅ፡-

“ሀገርና ሃይማኖት የሚያጠፋ ፣ ጠላት ባሕር ተሻግሮ መጥቷል። እኔም ያገሬ ሰው መድከሙን አይቼ እስካሁን ብታገስም ፣ እያለፈ እንደ ፍልፈል መሬት ይቆፍር ጀመር፤ አሁን ግን በእግዚአብሔር እርዳታ አገሬን አሳልፌ አልሰጠውም። ያገሬ ሰው ጉልበት ያለህ ተከተለኝ። ጉልበት የሌለህ በጸሎትህ እርዳኝ።”


@genius_acadamy
@genius_acadamy


🚨🌙 በሳውዲ አረቢያ ጨረቃ መታየቷን ተከተሎ የታላቁ የረመዳን ፆም ነገ ይጀመራል።


ረመዳን ሙባረክ 🌙

#RAMADAN1446


#Update #EXITEXAM

ነገ በዩኒቨርሲቲዎቻቹህ በኩል ታያላቹህ


የኢትዮጵያ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ህብረት ፕሬዝዳንት የሆነው ሃየሎም ስዩም የመውጫ ፈተና ውጤት ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሬጅስትራር መላኩንና ተፈታኞችም በተቋሞቻቸው በኩል ነገ ማየት እንደሚችሉ አሳውቋል።

@genius_acadamy
@genius_acadamy


#Exit_Exam_Result

ሀገር አቀፍ የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመውጫ ፈተና (Exit Exam) ውጤት ተለቋል።

https//:result.ethernet.edu.et ላይ በመግባት ExitExam የሚለውን በመምረጥና የራስዎን User Name በማስገባት ውጤትዎን መመልከት ይችላሉ።

በ2017 ዓ.ም አጋማሽ ዓመት የመውጫ ፈተና ከጥር 26-30/2017 ዓ.ም መሠጠቱ ይታወቃል።


የመውጫ ፈተና ውጤት ዛሬ ከሰዓት በኋላ ይፋ ይደረጋል።

የ2017 የመውጫ ፈተና ውጤት ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ይፋ እንደሚደረግ ከትምህርት ሚኒስቴር ምንጮቻችን ሰምተናል።

@genius_acadamy
@genius_acadamy




Exit Exam Schedule - Full ጥር 2017 ዓ.ም.xls
201.0Кб
#ExitExamSchedule

ሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተና ከጥር 26-30/2017 ዓ.ም ጀምሮ እንደሚሰጥ ይታወቃል፡፡

የፈተናው ሙሉ መርሐግብር (የሚሰጡ ፈተናዎች ዝርዝር፣ የፈተና ቀንና ሰዓት፣ የመፈተኛ ማዕከላት እንዲሁም የተፈታኞች ዝርዝር) ከላይ ተያይዟል፡፡

@genius_acadamy
@genius_acadamy


💶 በOnline ገንዘብ መስራት ይፍልጋሉ?💶


የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ከመጭው አመት ጀምሮ የዩንቨርስቲ ምርጫ ውስጥ ሊገባ ነው

የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ከ2018 ዓ.ም ጀምሮ የተማሪዎች የከፍተኛ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ምርጫ ውስጥ እንደሚገባ የትምህርት ሚኒስቴር ተናግሯል።

ዩኒቨርሲቲው እያከናወናቸው ላሉ ሥራዎች በጥናት ላይ የተመሰረተ ድጋፍ እንደሚያደርግ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ገልጿል። ከቀጣይ ዓመት ጀምሮም የተማሪዎች የከፍተኛ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ምርጫ ውስጥ የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲም እንደ አንድ አማራጭ እንደሚካተት ተጠቁሟል።

@genius_acadamy
@genius_acadamy


በዮኒቨርሲቲ ቆይታችሁ እነዚህ ነገሮች ብታረጉ ጥሩ ነው ❗️

💡....ዲያሪ መፃፍ .....

🎓 የካንፓስ ቆይታ በጣም የሚገርሙ moment ያሉበት ነው ።በቃ 3 or 5 የደስታ ዘመናት ... የሚገራርም ሰው ታያላችሁ ....የሚወዛገብ ፤ የሚወሳሰብ የሚፈላሰፍ ፤ ምንም ዲጭ የማይልበት  ፤ ተንከሲሲስ ፤ በጣም ጅል ፤ አራዳ ነኝ ባይ ገገማ ....ኧረ ምኑ ቅጡ ....በህይወታችን አዳዲስ ነገሮች ይከሰታሉ ። ነገር ግን እንረሳቸዋለን ቶሎ ቶሎ አዳዲስ ነገር ስለሚፈጠሩ ይረሳል ። እናንተ ደግሞ ከፈለጋችሁ መፃፍ ብታረጉት ፤ ወደፊት ፊልም የመስራት ዕቅድ ካላችሁ ሚገራርሙ ገፀባህራያት ታገኛላቹሁ....ብቻ በላይፋቹ የማታገኙት ዕድል ስለሆነ በርትታቹሁ?...አዳዲስ ነገር ሲኖር በወረቀት (ዲያሪ)  "ወይም ስልካቹም ላይ ቢሆን አስፍሩት ..! ትዝታዎቻቹ ናቸው እንዳትረሱት...ሙድ የተያዘባችሁ ሙድ የያዛችሁትን ...የሚያስቅ ፤ የሚያሳዝን፤ የሚያናድድ ብቻ ....ቸክችኩ ቢያንስ ልጆቻችሁ ትሰጧቹሃላቹ እነሱም ካምፓስ ሊገቡ ሲሉ ....በየቀኑ ሳይሆን የሆነ ነገር ሲፈጠር ፃፉት ...አሁን ምንም ላይመስላቹሁ ይችላል ግን አልፎ ስታዩት  የምርም ትደሰታላቹሁ .....

💡አዲስ ቋንቋ መማር ......❗️

📚 ዶርም የምትሰባሰቡት ከየአቅጣጫው ነው ። ብዙ የማታውቁትን የሚያቁ ይሄም አለ❓...  ያምሃል...!  የሚያስብሉ ዕውቀቶች ታገኛላችሁ ። አንዱ ደሞ ቋንቋ ነው ። በተለይ ኢትዮጵያ ውስጥ በርከት ያለ ተናጋሪ ያላቸው እንደ ኦሮሚኛ ፣ሲዳመኛ ፣ትግረኛ፣ ሱማሌኛ ቋንቋዎች የሚችሉ ልጆች ዶርም ካገኛችሁ በቀን 5 ቃልም ቢሆን ቀስ እያላችሁ ተማሩ .....የምር ይጠቅማቹሃል ። ቋንቋ መልመድ ጥሩ ነው ። ሁላቹም ጋር አዲስ ቋንቋ ከሌለ ደሞ ጓደኞቻችሁን የምታስታውሱበት አለ ኣ በቃ ....አዲስ የባህርማዶ አንድ ቋንቋ በጋራ ተለማመዱ ...ስፓንሽ ወይ ደሞ ፈረንች ...የተመቻችሁ በጋራ በቀን ትንሽ ነገር አጥኑ ። የ3 or 5 አመት ጓደኞቻችሁን ስትለዮዎቸው ማስታወሻ ይሆናቹሃል ። ፈታ እያላችሁ ጠዋት ላይ 5 ቃላት ምናምን ሸምድዱ የምርም ጓደኝነታችሁ ለማጠንከር ያግዛቹሃል ።

💡መክሊታችሁን ማዳበር ......!

📚 የሰው ልጅ በተፈጥሮ የተለያዩ መክሊቶች ተሰጥቶታል ። ታዲያ እናንተም የተፈጥሮ ስጦታችሁን በክበብ በመሳተፍ ማሳደግ አለባቹሁ፣ በገገሙ ትምህርት ብቻ ካንሰር ነው  የሚሆንባቹሁ ...ትወና የምትሞክሩ....ግጥም መጣጥፍ የምትሞክሩ ....ስዕል ....ሃይማኖታዊ ነገሮች የምትሞክሩ  ብቻ ግቢ ላይ ብዙ ክበቦች አሉ ...የሴቶች ...የበጎአድራጎት ...የሌለ የለም ....እና ተሳተፉ ማህበር  አለ ...ዕቁብ፣ ዕድር ሁላ አለ (ቀልዴ ነው ...) ....በቃ በዓል ግዜ ደስ ይላል ። የምትወዱት ከኖርማል ትምህርታቹ ላይ የሚደበል ...ዘፈን ከሆነ ...ስፓርት ከሆነ ...ኳስ ከሆነ .....ብቻ የምትወዱትን አንድ ነገር አዳብሯቹሁ ። ተገኙ .....በገገሙ ትምሮ ብቻ አይነፋም ...!


💡 የተለያዮ EVENT እና TOUR  እንዳትቀሩ ...

በግቢ ቆይታ ፍራንክ ባይኖራቹ ራሱ ተበዳድራቹ  ሀገር መጎብኘት አሪፍ ነው ። በቃ ceremony  ሲኖር ....ይሂዱ ባክህ አትበሉ ዳግም የሚገኝ ነገር አይደለም ጦቢያን የምር የምታውቁበት ነው ። ትምህርተ ጋር ካልተጋጨ በየ ግዜው  በአስተባሪዎች ጉዞ ይኖራል ። ስለዚህ.... አትቅሩ ...የመፅሀፍ ምረቃዎች ....አነቃቂ ንግሮች ...ትያአታራዊ ዝግጅቶች ይደረጋሉ .....አትቅሩ ....ታዋቂ ሰዎች በየግቢ እየመጡ በተለይ ወጣቶች የህይወት ልምዶቻቸውን ስለሚያጋሩ .....የምታደንቋቸው ሰዎች በየትኛው መንገድ ነው የተሳካላቸው ....የሚለው የህይወት ጉዞን ትማሩበታላቹሁ ...የፈታ ኢቨንቶችም አሉ በቃ ....ፈተና ሲያልቅ ምናምን ከች የሚሉ እና ሳትንዘላዘሉ ተሳተፉ ....እነ ሮፍናን ደግሰው መቼስ አይቀርም .....እነ እሸቱ መለሰ እየቀለዱ መቅረት ይከብዳል ....


⏰️ አዳዲስ ነገሮች ሞክሩ ...አትፍሩ

📚 አዳዲስ ነገሮች የማድረግ ዕድሉ ስለሚኖረን ምንአቧቱ በእናት ሆድ አይለመድ አትፍሩ ሞክሩ ....ታዲያ ሱስ ምናምን ሳይሆን አሪፍ የሚባሉ ነገሮች የፍቅር ህይወትም ቢሆን ትምህርትን በማይነካ መልኩ ቢደረግ አይከፋም (ታዲያ ለሴሚስተር የሚቆይ ሳይሆን የምር መሆኑኑን ካመናችሁ ..) ....በግ ተራም ቢሆን አንዳንዴ መሄዱ ለክፉ አይሰጥም (አመራችሁ ዴ ቀልዴ ነው..)  .....ሀገራቹ ሄዳቹሁ ለማውራትም ኮ መሞከሩ አይከፋም ።ግን ብዙ አትንዘላዘሉ ...ቸክሉ ...በቃ የሚያስደስታችሁን አዲስ ነገር ሞክሩ .....ብዙዎች ካንፓስ ሃይማኖተኛ ያረጋቸዋል አንዳንዶች ደሞ ...."ፈላስፈ አንዳነዶች ....ዘልዛላም ይሆናል ....አንዳንዴ ሳታስቡት ሃርድ ውስጥ ትገቡ ይሆናል ....ታዲያ ያን ግዜ አትጨናነቁ ...Normal ነው ። በተረፈ መልካም ካንፓስ!

💬በመጨረሻም ካንፓስ ላይ ቆይታቹሁ ልትደሰቱበት የሚችሉበትን የማትፀፀቱበትን ነገር ብቻ ከውኑ ። በቃ ያማረ የግቢ ቆይታ እንዲሆንላቹ ምኞቴ ነው ። ጥሩ ጥሩ ነገሮች ሊያውም የማይደገሙ ሲያጋጥማቹሁ አትለፉ እርግጥ ዋናው ጉዳያቹሁ ትምህርት ቢሆንም ...መደሰቱ መሳተፉ አይከፋም ። አይዞን በቆንጆ ሁኔታ ይታለፋል ።

@genius_acadamy
@genius_acadamy


1GB ስንት MB ነው?

Показано 20 последних публикаций.