በአንድ ወቅት ነቢ ሱለይማን ዐለይሂ ሰላም አንዲት ጉንዳን ከድንጋይ መሃል ያገኛሉ ። ጉንዳኗም አብሯት አንድ ፍሬ ስንዴ አጠገቧ ነበር ። ነቢ ሱለይማንም " እዚህ ድንጋይ መሃል እየኖርሽም አሏህ ይረዝቅሻልን ? " ብሎ ይጠይቋታል ። እርሷም " አዎን አሏህ ምን ይሳነዋል ? " ብላ መለሰች ። ለመሆኑ ይህች አንዷ የስንዴ ፍሬ ለምን ያክል ጊዜ ትበቃሻለች " ሲሉም ይጠይቋታል ። እርሷም " ለአንድ ዓመት ይበቃኛል !! " ስትል መለሰች ነቢዩ ሱለይማንም ዐለይሂ ሰላም " እስቲ እኔ ዘንድ ለአንድ አመት ላቆይሽ " ብለው በመውሰድ አንድ የስንዴ ፍሬ ሰጥተው ያስቀምጧታል።
በአመቱም ጉዷን ለማየት ወዳለችበት ሲሄዱ ግማሹን የስንዴ ፍሬ በልታ ግማሹን አስቀምጣዋለች ። ነብዩ ሱለይማይን ተደንቀው " ለአንድ ዓመት አንድ የስንዴ ፍሬ ይበቃኛል ብለሽኝ አልነበረምን ታዲያ ግማሹን በልተሽ ግማሹን ለምን ተውሽው ? " ሲሉ በአግራሞት ይጠይቋታል ። እርሷም " መጀመሪያ ለአንድ አመት አንድ ፍሬ ስንዴ ይበቃኛል ያልኩት እኮ በአሏህ እጅ ላይ ሆኜ ነው !! አሁን ግን ባንተ እጅ ስለገባሁ ሰው ነክና ልትረሳኝ ትችላለክ ብዬ ግማሹን በልቼ ግማሹን ደግሞ ለምናልባት ብዬ አስቀረሁት " ስትል መለሰችለት ።
ተወኩልን ከጉንዳን ተማር ሪዝቅህ በአሏህ እጅ እንደሆነ እወቅ።
@heppymuslim29
በአመቱም ጉዷን ለማየት ወዳለችበት ሲሄዱ ግማሹን የስንዴ ፍሬ በልታ ግማሹን አስቀምጣዋለች ። ነብዩ ሱለይማይን ተደንቀው " ለአንድ ዓመት አንድ የስንዴ ፍሬ ይበቃኛል ብለሽኝ አልነበረምን ታዲያ ግማሹን በልተሽ ግማሹን ለምን ተውሽው ? " ሲሉ በአግራሞት ይጠይቋታል ። እርሷም " መጀመሪያ ለአንድ አመት አንድ ፍሬ ስንዴ ይበቃኛል ያልኩት እኮ በአሏህ እጅ ላይ ሆኜ ነው !! አሁን ግን ባንተ እጅ ስለገባሁ ሰው ነክና ልትረሳኝ ትችላለክ ብዬ ግማሹን በልቼ ግማሹን ደግሞ ለምናልባት ብዬ አስቀረሁት " ስትል መለሰችለት ።
ተወኩልን ከጉንዳን ተማር ሪዝቅህ በአሏህ እጅ እንደሆነ እወቅ።
@heppymuslim29