በተማሪ ወላጅ ትስስር ለተማሪ ግዛቸው ተሻለ የላፕቶፕ ኮምፒውተር እና የአልባሳት ድጋፍ ተደረገለት፡፡
በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ አካቶ ትግበራ ሥራ አስፈጻሚ ከሚከናወኑ ተግባራት አንዱ በሆነው በተማሪ ወላጅ ትስስር የህክምና ሳይንስ ተማሪ ግዛቸው ተሻለ ከአቶ መኩሪያ ጎሼ የላፕቶፕ እና አልባሳት ድጋፍ ተደርጎለታል፡፡
የዩኒቨርሲቲው የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ አካቶ ትግበራ ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ባንቻለም ካሴ ክፍሉ ከሚሰራቸው ተግባራት መካከል ኢኮኖሚያዊ ችግር ያለባቸውን ተማሪዎች ለይቶ አስፈላጊውን ድጋፍ እና ክትትል ማድረግ መሆኑን ጠቅሰው ሥራው የሚከናወነውም በጎ ፈቃደኛ የሆኑ አካላትን ጋር ትስስር በመፍጠር ለተማሪዎች አስፈላጊ የሆኑ ቁሳቁሶችን በማሟላት ትምህርታቸውን በአግባቡ እንዲማሩ ማድረግ ነው ብላዋል፡፡
ቀደም ሲል በዚህ ሂደት የተለዩትን ተማሪዎች ከበጎ ፈቃደኛ ወላጆች ጋር የተማሪ ወላጅ ትስስር በመፍጠር ኢኮኖሚያዊ ችግር ያለባቸው ተማሪዎች በተደረገላቸው ድጋፍ መመረቃቸውን ተናግረዋል፡፡ አያይዘውም አሁንም ቢሆን ከ400 በላይ ድጋፍን የሚፈልጉ ተማሪዎች ያሉ በመሆናቸው በዚህ በጎ ተግባር ሁሉም ሰው እንዲሳተፍ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡
ድጋፉን ያደረጉት አቶ መኩሪያው ዛሬ ካደረጉት ድጋፍ በተጨማሪ ተማሪ ግዛቸው ትምህርቱን አስከሚያጠናቅቅ ድረስ በየወሩ 500 ብር እና በአስፈላጊ ነገሮች ሁሉ አግዘው እንደሚያስመርቁት ቃል ገብተዋል፡፡ ድጋፉን የአካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝደንት አእምሮ ታደሰ (ዶ/ር) በተገኙበት አስረክበዋል፡፡
ጥር 26/2017 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ አካቶ ትግበራ ሥራ አስፈጻሚ ከሚከናወኑ ተግባራት አንዱ በሆነው በተማሪ ወላጅ ትስስር የህክምና ሳይንስ ተማሪ ግዛቸው ተሻለ ከአቶ መኩሪያ ጎሼ የላፕቶፕ እና አልባሳት ድጋፍ ተደርጎለታል፡፡
የዩኒቨርሲቲው የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ አካቶ ትግበራ ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ባንቻለም ካሴ ክፍሉ ከሚሰራቸው ተግባራት መካከል ኢኮኖሚያዊ ችግር ያለባቸውን ተማሪዎች ለይቶ አስፈላጊውን ድጋፍ እና ክትትል ማድረግ መሆኑን ጠቅሰው ሥራው የሚከናወነውም በጎ ፈቃደኛ የሆኑ አካላትን ጋር ትስስር በመፍጠር ለተማሪዎች አስፈላጊ የሆኑ ቁሳቁሶችን በማሟላት ትምህርታቸውን በአግባቡ እንዲማሩ ማድረግ ነው ብላዋል፡፡
ቀደም ሲል በዚህ ሂደት የተለዩትን ተማሪዎች ከበጎ ፈቃደኛ ወላጆች ጋር የተማሪ ወላጅ ትስስር በመፍጠር ኢኮኖሚያዊ ችግር ያለባቸው ተማሪዎች በተደረገላቸው ድጋፍ መመረቃቸውን ተናግረዋል፡፡ አያይዘውም አሁንም ቢሆን ከ400 በላይ ድጋፍን የሚፈልጉ ተማሪዎች ያሉ በመሆናቸው በዚህ በጎ ተግባር ሁሉም ሰው እንዲሳተፍ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡
ድጋፉን ያደረጉት አቶ መኩሪያው ዛሬ ካደረጉት ድጋፍ በተጨማሪ ተማሪ ግዛቸው ትምህርቱን አስከሚያጠናቅቅ ድረስ በየወሩ 500 ብር እና በአስፈላጊ ነገሮች ሁሉ አግዘው እንደሚያስመርቁት ቃል ገብተዋል፡፡ ድጋፉን የአካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝደንት አእምሮ ታደሰ (ዶ/ር) በተገኙበት አስረክበዋል፡፡
ጥር 26/2017 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ