የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአርማውን ቀለም የመቀየር ፍላጎትና እቅድ እንደሌለው ለመሠረት ሚድያ አሳወቀ
- የድርጅቱ አዲስ አጥር ላይ በአረንጓዴ ቀለም ብቻ የሰፈረው አርማ መልሶ ሊቀባ መሆኑ ታውቋል
(መሠረት ሚድያ)- ከሰሞኑ በርካታ የማህበራዊ ሚድያ ተጠቃሚዎች የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቅርቡ በቪ አይ ፒ መግቢያ አካባቢ ባሰራው አጥር ላይ የሚታወቅበት አረንጓዴ፣ ቢጫ እና ቀይ ቀለም ቀርቶ በአረንጓዴ ቀለም ብቻ አርማው (ሎጎው) ተቀብቶ በመመልከታቸው የተለያየ አስተያየት ሲሰነዝሩ ተስተውሏል።
አንዳንዶች አየር መንገዱ ቀስ በቀስ የአርማውን ቀለም እየቀየረ እንደሆነ የገመቱ ሲሆን ድርጊቱን በተለያየ መልኩ ሲገልፁት ታይቷል።
መሠረት ሚድያ በዚህ ዙርያ አየር መንገዱን ያነጋገረ ሲሆን ተቋሙ አርማውን የመቀየር ፍላጎትና እቅድ እንደሌለው አሳውቋል።
"ይሄ የእኛ እቅድም፣ ፍላጎትም አይደለም" ያሉን አንድ የአየር መንገዱ ሀላፊ አዲሱ አጥር በአረንጓዴ ብቻ የተቀባው ገፅታውን 'ቀለል ያለ' እንዲሆን ለማድረግ ነው ብለዋል።
"በዚህ ዙርያ ተወያይተንበታል፣ ብዙ ግርታም እንደፈጠረ አስተውለናል። ወደቀደመው እና ወደ ኦፊሴላዊው የአርማ ቀለሞች መልሶ በቅርቡ ይቀባል" በማለት አስተያየት ሰጥተዋል።
አንድ ሌላ የዘርፉ ባለሙያ በሰጠን አስተያየትም አንዳንድ ግዜ ባለ ቀለም ሎጎዎች ቀለል ያለ መልክ እንዲኖራቸው ሲፈለግ ቅርፃቸውን ጠብቀው ቀለማቸው ሊቀየር እንደሚችል ጠቁሟል።
"ለምሳሌ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በታላቁ ሩጫ ቲሸርቶች ላይ ያለውን ሎጎ ብናይ ወይ ነጭ ወይ ሌላ ቀለም ነው፣ አላማው ዲዛይኑ የማይረብሽ እና ቀለል ያለ እንዲሆን ነው። ይህ አሰራር እንደ አሜሪካ ባሉ ሀገራት በጣም የተለመደ አሰራር ነው" በማለት ሙያዊ አስተያየቱን ሰጥቷል።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
- የድርጅቱ አዲስ አጥር ላይ በአረንጓዴ ቀለም ብቻ የሰፈረው አርማ መልሶ ሊቀባ መሆኑ ታውቋል
(መሠረት ሚድያ)- ከሰሞኑ በርካታ የማህበራዊ ሚድያ ተጠቃሚዎች የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቅርቡ በቪ አይ ፒ መግቢያ አካባቢ ባሰራው አጥር ላይ የሚታወቅበት አረንጓዴ፣ ቢጫ እና ቀይ ቀለም ቀርቶ በአረንጓዴ ቀለም ብቻ አርማው (ሎጎው) ተቀብቶ በመመልከታቸው የተለያየ አስተያየት ሲሰነዝሩ ተስተውሏል።
አንዳንዶች አየር መንገዱ ቀስ በቀስ የአርማውን ቀለም እየቀየረ እንደሆነ የገመቱ ሲሆን ድርጊቱን በተለያየ መልኩ ሲገልፁት ታይቷል።
መሠረት ሚድያ በዚህ ዙርያ አየር መንገዱን ያነጋገረ ሲሆን ተቋሙ አርማውን የመቀየር ፍላጎትና እቅድ እንደሌለው አሳውቋል።
"ይሄ የእኛ እቅድም፣ ፍላጎትም አይደለም" ያሉን አንድ የአየር መንገዱ ሀላፊ አዲሱ አጥር በአረንጓዴ ብቻ የተቀባው ገፅታውን 'ቀለል ያለ' እንዲሆን ለማድረግ ነው ብለዋል።
"በዚህ ዙርያ ተወያይተንበታል፣ ብዙ ግርታም እንደፈጠረ አስተውለናል። ወደቀደመው እና ወደ ኦፊሴላዊው የአርማ ቀለሞች መልሶ በቅርቡ ይቀባል" በማለት አስተያየት ሰጥተዋል።
አንድ ሌላ የዘርፉ ባለሙያ በሰጠን አስተያየትም አንዳንድ ግዜ ባለ ቀለም ሎጎዎች ቀለል ያለ መልክ እንዲኖራቸው ሲፈለግ ቅርፃቸውን ጠብቀው ቀለማቸው ሊቀየር እንደሚችል ጠቁሟል።
"ለምሳሌ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በታላቁ ሩጫ ቲሸርቶች ላይ ያለውን ሎጎ ብናይ ወይ ነጭ ወይ ሌላ ቀለም ነው፣ አላማው ዲዛይኑ የማይረብሽ እና ቀለል ያለ እንዲሆን ነው። ይህ አሰራር እንደ አሜሪካ ባሉ ሀገራት በጣም የተለመደ አሰራር ነው" በማለት ሙያዊ አስተያየቱን ሰጥቷል።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia