አንዳንድ እድሜያቸው የገፋ መኪናዎች ወደ ቦሌ አቅጣጫ እንዳይንቀሳቀሱ እየተደረጉ እንደሆነ ታወቀ
(መሠረት ሚድያ)- ከአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ጋር በተያያዘ አንዳንድ እድሜ ጠገብ የሆኑ ተሽከርካሪዎች ወደ ቦሌ አቅጣጫ የመንቀሳቀስ እገዳ እየተደረገባቸው እንደሆነ ታውቋል።
ከባለፈው አርብ እለት ጀምሮ በርካታ የእነዚህ ተሽከርካሪዎች ባለቤቶች ለመሠረት ሚድያ ባደረሱት ጥቆማ ከቦሌ ብስራስ፣ ቦሌ አትላስ፣ ከአራት ኪሎ እና ከኡራኤል አቅጣጫዎች በመነሳት ወደ ዋናው የቦሌ መንገድ (በኦፊሴላዊ አጠራሩ የአፍሪካ ጎዳና) ሲጓዙ በትራፊክ ተቆጣጣሪዎች እንዲመለሱ መታዘዛቸውን አስረድተዋል።
"ዝርዝር የማስፈፀሚያ ህግ ባልወጣበት እንዲህ አይነት እገዳ መጣሉ የህግ የበላይነት አለመኖሩን ማሳያ ነው" ያሉ አንድ እገዳው ያጋጠማቸው አሽከርካሪ ድርጊቱን ኮንነዋል።
ሌላ አሽከርካሪ ደግሞ "አላማው ምንድነው? ዜጎቻችን በሙሉ የሚነዱት ዘመናዊ ተሽከርካሪ ነው የሚል መልእክት ለማስተላለፍ ይሆን?" በማለት ጥያቄያቸውን ሰንዝረዋል።
እገዳውን እየጣሉ ያሉት የትራፊክ ፖሊሶች ዝርዝር ማስፈፀምያ ደርሷቸው ይሆን ወይስ በራሳቸው ተነሳሽነት የፈፀሙት ነው የሚለውን ለማጣራት ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም።
በአዲስ አበባ አሮጌ መኪናዎች በተለይ የኮሪደር ልማት በተሰራባቸው ቦታዎች እንዳይንቀሳቀሱ ክልከላ ሊደረግባቸው እንደሚችል በመጀመርያ የተሰማው የዛሬ አመት ገደማ ነበር።
በወቅቱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ያብባል አዲስ የአሮጌ መኪና ባለቤቶች መኪናቸውን መቀየር ካልቻሉ በለሙ የኮሊደር መንገዶች ላይ እንዳይንቀሳቀሱ ክልከላ ሊደረግባቸው ይችላል ብለው ለሚድያዎች ተናግረው ነበር።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
(መሠረት ሚድያ)- ከአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ጋር በተያያዘ አንዳንድ እድሜ ጠገብ የሆኑ ተሽከርካሪዎች ወደ ቦሌ አቅጣጫ የመንቀሳቀስ እገዳ እየተደረገባቸው እንደሆነ ታውቋል።
ከባለፈው አርብ እለት ጀምሮ በርካታ የእነዚህ ተሽከርካሪዎች ባለቤቶች ለመሠረት ሚድያ ባደረሱት ጥቆማ ከቦሌ ብስራስ፣ ቦሌ አትላስ፣ ከአራት ኪሎ እና ከኡራኤል አቅጣጫዎች በመነሳት ወደ ዋናው የቦሌ መንገድ (በኦፊሴላዊ አጠራሩ የአፍሪካ ጎዳና) ሲጓዙ በትራፊክ ተቆጣጣሪዎች እንዲመለሱ መታዘዛቸውን አስረድተዋል።
"ዝርዝር የማስፈፀሚያ ህግ ባልወጣበት እንዲህ አይነት እገዳ መጣሉ የህግ የበላይነት አለመኖሩን ማሳያ ነው" ያሉ አንድ እገዳው ያጋጠማቸው አሽከርካሪ ድርጊቱን ኮንነዋል።
ሌላ አሽከርካሪ ደግሞ "አላማው ምንድነው? ዜጎቻችን በሙሉ የሚነዱት ዘመናዊ ተሽከርካሪ ነው የሚል መልእክት ለማስተላለፍ ይሆን?" በማለት ጥያቄያቸውን ሰንዝረዋል።
እገዳውን እየጣሉ ያሉት የትራፊክ ፖሊሶች ዝርዝር ማስፈፀምያ ደርሷቸው ይሆን ወይስ በራሳቸው ተነሳሽነት የፈፀሙት ነው የሚለውን ለማጣራት ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም።
በአዲስ አበባ አሮጌ መኪናዎች በተለይ የኮሪደር ልማት በተሰራባቸው ቦታዎች እንዳይንቀሳቀሱ ክልከላ ሊደረግባቸው እንደሚችል በመጀመርያ የተሰማው የዛሬ አመት ገደማ ነበር።
በወቅቱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ያብባል አዲስ የአሮጌ መኪና ባለቤቶች መኪናቸውን መቀየር ካልቻሉ በለሙ የኮሊደር መንገዶች ላይ እንዳይንቀሳቀሱ ክልከላ ሊደረግባቸው ይችላል ብለው ለሚድያዎች ተናግረው ነበር።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia