ኦርቶዶክሳውያን እህቶቻችን አላችሁ አይደል
አቢሲኒያ ባንክ ያለ ዋስትና 55 ሚሊየን ብር የብድር አገልግሎት ለሴት ደንበኞቹ መስጠቱን ገለጸ
👉ባንኩ የዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን አስመልክቶ "እችላለው" የተሰኘ የሴቶች የተሰጥዖ ውድድር አዘጋጅቷል
የካቲት 25/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) አቢሲኒያ ባንክ ለሴት ሥራ ፈጣሪ ደንበኞቹ ከ55 ሚሊየን ብር በላይ የብድር አገልግሎት ያለምንም ማስያዣና ዋስትና መስጠቱን አስታውቋል።
የብድር አገልግሎቱ ባለፉት ሦስት ዓመታት ለ125 ሴት ደንበኞች የተሰጠ መሆኑን የገለጹት የባንኩ ዋና መስሪያ ቤት የደንበኞች ሂሳብ አገልግሎት ባለሙያ ሄለን ግርማ ናቸው።
ይህን መሰል አገልግሎት የሚሰጠው ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን አስመልክቶ መሆኑን የገለጹ ሲሆን፤ ሴቶችን ለማበረታት እና ለማገዝ መሆኑን አንስተዋል።
በዚህም የዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን አስመልክቶ "እችላለው" በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀውን ውድድር በመሳተፍ በአነስተኛ የወለድ መጠን እስከ መጋቢት 22 ቀን 2017 ዓ.ም በዚህ ዓመት ያለ ማስያዣ የብድር አገልግሎት የሚሰጥበት ሁኔታ መኖሩን ገልጸዋል።
በዚህም በውድድር ተሳትፈው አሸናፊ ለሚሆኑ 50 ሴቶች በአነስተኛ ወለድ ያለማስያዣ እስከ 500 ሺሕ ብር ድረስ የብድር አገልግሎት የሚሰጥ መሆኑን ጠቁመዋል።
እንዲሁም ከብድር አገልግሎቱ በተጨማሪ ሴቶች መስራት በሚፈልጉት ዘርፍ ላይ የሥራ ፕሮፖዛል ቢያስገቡ፤ ሥራውን የተመለከተ ስልጠናዎች እንደሚመቻቹ አክለው ለአሐዱ ገልጸዋል።
የዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን አስመልክቶ ለሴቶች የተዘጋጀው ውድድር ትናንት የካቲት 24 ቀን 2017 ዓ.ም የጀመረ ሲሆን፤ ማስረከቢያ ቀኑ መጋቢት 8 ቀን ይጠናቀቃል ተብሏል።
በባንኩ ለ4ተኛ ጊዜ በተዘጋጀው የ"እችላለሁ" መርሐ ግብር፤ በሙዚቃ (በድምጽ)፣ በቲክቶክ ቪዲዮ እና በሥራ ፈጠራ ውድድሮች ላይ ተሰጥዖ ያላቸው እንስቶች እንዲሳተፉም ጥሪ ቀርቧል፡፡
በቲክቶክ ቪዲዮ የተሰጥዖ ውድድር ባንኩ ለሴት ደንበኞቻችን ያዘጋጃቸውን 'አደይ' እና 'ዘሃራ' የቁጠባ ሒሳብ አገልግሎቶችን በተለየ መንገድ የሚያስተዋወቅ መሆን ይኖርበታል ሲልም ባንኩ አስታውቋል፡፡
በፍርቱና ወልደአብ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ
አቢሲኒያ ባንክ ያለ ዋስትና 55 ሚሊየን ብር የብድር አገልግሎት ለሴት ደንበኞቹ መስጠቱን ገለጸ
👉ባንኩ የዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን አስመልክቶ "እችላለው" የተሰኘ የሴቶች የተሰጥዖ ውድድር አዘጋጅቷል
የካቲት 25/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) አቢሲኒያ ባንክ ለሴት ሥራ ፈጣሪ ደንበኞቹ ከ55 ሚሊየን ብር በላይ የብድር አገልግሎት ያለምንም ማስያዣና ዋስትና መስጠቱን አስታውቋል።
የብድር አገልግሎቱ ባለፉት ሦስት ዓመታት ለ125 ሴት ደንበኞች የተሰጠ መሆኑን የገለጹት የባንኩ ዋና መስሪያ ቤት የደንበኞች ሂሳብ አገልግሎት ባለሙያ ሄለን ግርማ ናቸው።
ይህን መሰል አገልግሎት የሚሰጠው ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን አስመልክቶ መሆኑን የገለጹ ሲሆን፤ ሴቶችን ለማበረታት እና ለማገዝ መሆኑን አንስተዋል።
በዚህም የዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን አስመልክቶ "እችላለው" በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀውን ውድድር በመሳተፍ በአነስተኛ የወለድ መጠን እስከ መጋቢት 22 ቀን 2017 ዓ.ም በዚህ ዓመት ያለ ማስያዣ የብድር አገልግሎት የሚሰጥበት ሁኔታ መኖሩን ገልጸዋል።
በዚህም በውድድር ተሳትፈው አሸናፊ ለሚሆኑ 50 ሴቶች በአነስተኛ ወለድ ያለማስያዣ እስከ 500 ሺሕ ብር ድረስ የብድር አገልግሎት የሚሰጥ መሆኑን ጠቁመዋል።
እንዲሁም ከብድር አገልግሎቱ በተጨማሪ ሴቶች መስራት በሚፈልጉት ዘርፍ ላይ የሥራ ፕሮፖዛል ቢያስገቡ፤ ሥራውን የተመለከተ ስልጠናዎች እንደሚመቻቹ አክለው ለአሐዱ ገልጸዋል።
የዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን አስመልክቶ ለሴቶች የተዘጋጀው ውድድር ትናንት የካቲት 24 ቀን 2017 ዓ.ም የጀመረ ሲሆን፤ ማስረከቢያ ቀኑ መጋቢት 8 ቀን ይጠናቀቃል ተብሏል።
በባንኩ ለ4ተኛ ጊዜ በተዘጋጀው የ"እችላለሁ" መርሐ ግብር፤ በሙዚቃ (በድምጽ)፣ በቲክቶክ ቪዲዮ እና በሥራ ፈጠራ ውድድሮች ላይ ተሰጥዖ ያላቸው እንስቶች እንዲሳተፉም ጥሪ ቀርቧል፡፡
በቲክቶክ ቪዲዮ የተሰጥዖ ውድድር ባንኩ ለሴት ደንበኞቻችን ያዘጋጃቸውን 'አደይ' እና 'ዘሃራ' የቁጠባ ሒሳብ አገልግሎቶችን በተለየ መንገድ የሚያስተዋወቅ መሆን ይኖርበታል ሲልም ባንኩ አስታውቋል፡፡
በፍርቱና ወልደአብ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ