ዳግማዊ አጤ ምኒልክ ንጉሠ ነገሥት ዘ ኢትዮጵያ! 👑
የመላ ጥቁር ሕዝብ ድል የሆነውን የዓድዋን ጦርነት መርተው በድል ያጠናቀቁ መሆናቸው ብቻ አይደለም በዚህ ታሪካዊ ዕለት መወሳት ያለበት።
💥 ኢትዮጵያ እንደ ሀገር አሁን የያዘችውን ቅርጽ ትይዝ ነበር ወይ?
💥 ለሀገራችን እንግዳ የሆኑ በርካታ ተቋማት እና ወሳኝ አገልግሎቶች 20 ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ማግኘት ይቻል ነበር ወይ?
💥 ዘመናዊ አመራር እና አስተዳደር በአጭር ጊዜ እንዲዋሃደን ማድረግ ይቻል ነበር ወይ?
💥 20 ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ባህልን እና ኃይማኖትን ሳይለቅ (without compromising religious and cultural values) አስተሳሰብን በዚያ ደረጃ መቀየር ይቻል ነበር ወይ?
💥 ከጦርነት እና ግጭት በላይ ዲፕሎማሲን የማስቀደም ልምድ ይኖረን ነበር ወይ?
💥 የሴቶችን ሚና ወሳኝነት እንቀበል/እንርረዳ ነበር ወይ?
💥 ዓለማቀፍ ጉዳዮች (የውጪ ጉዳይ)ን የተያዙበትን ጥበብ መማር ይቻል ነበር ወይ?
(ጨምሩበት)።
ዳግማዊ አጤ ምኒልክ ን/ነ ዘ ኢትዮጵያ ዓለምን ከቀየሩ ጥቂት ክስተቶች አንዱ የሆነው የጥቁር ሕዝቦች ድል፣ የዓድዋ ድል ምልክት፣ የዘመናዊ አስተሳሰብ ፋና ወጊ እና ሀገር ወዳድ ምርጥ ''ጥቁር'' መሪ ነበሩ።
ክብር ለእርሳቸው እና በዓድዋ ጦርነት ተሳትፈውና ተሰውተው ነፃ ሀገር ላቆዩልን አባትና እናቶቻችን ይሁን! እንዲሁም ታሪኩን ብቻ ሰምቶ በመላው ዓለም በየዓመቱ በኩራት ለሚዘክረው ጥቁር ሕዝብ!
መልካም የዓድዋ ድል በዓል!
Hawlet Ahmed