አዝ፦ የእግዚአብሔር እጅ የያዘው ነገር
እንዳይወድቅ አይፈራ እንዳይጠፋ አይፈራ
ከጥላው ሥር ያረፈው ሰው
ዘለዓለሙ አያሰጋው (2x)
አባትዬ የእኔ ወዳጅ (2x)
ኑሮዬ በአንተ እጅ (2x)
አባትዬ የእኔ ከለላ ከለላዬ
በጥላህ ሥር ነው ማደሪያዬ (2x)
በእናቴ ማህፀን ደምሳለ ሆኜ አጥንቶቼም ሳይዋደዱ
አንተው ታውቀው ነበር እንዲህ እንዲሆን የሕይወቴ አካሄዱ
ደግሞ እስከ አሳለፍከኝ በቸርነትህ የትላንቱኑ ጨለማ
ለነገውስ ቢሆን ለምን አላምንም ሕይወቴ በእጅህ ነውና
ተውኩት ሁሉንም ለአንተ ተውኩት
ተይ ነፍሴ እኔ አላውቅም ብዬ እንዳልኩት
ይሁን ያልከው የፀና ለመሆኑ
ምስክር ነው ሰማይ የለም አገር መሆኑ
አዝ፦ የእግዚአብሔር እጅ የያዘው ነገር
እንዳይወድቅ አይፈራ እንዳይጠፋ አይፈራ
ከጥላው ሥር ያረፈው ሰው
ዘለዓለሙ አያሰጋው (2x)
አባትዬ የእኔ ወዳጅ (2x)
ኑሮዬ በአንተ እጅ (2x)
አባትዬ የእኔ ከለላ ከለላዬ
በጥላህ ሥር ነው ማደሪያዬ (2x)
ክብርን የምትገልፅበት ደካማ ሰው ስትፈልግ አገኘኸኝ
እንጂማ በእራሴ እንኳን በአንተ በሰውም ዓይን የማልሞላ ነኝ
ገና በወደድከኝ በንጋት አየሁ ብልስ ምን እልሃለሁ
አንተ ነህ ደጀኔ ተባረክልኝ ከትከሻህ የሚያወርደኝ ማነው
አልጥልሽ አልተውሽ እያልክ
ልፌ ስትደግፈኝ እንደዋልክ
አይቼህ መንፈሴ ረካ
አትተወኝም አትረሳኝም ለካ
አዬ አትረሳኝም ለካ
አትተወኝም በቃ አትረሳኝም በቃ
አሄ አትረሳኝም በቃ
አትተወኝም በቃ አትለቀኝም በቃ
አሄ አትለቀኝም በቃ (2x)
እንዳይወድቅ አይፈራ እንዳይጠፋ አይፈራ
ከጥላው ሥር ያረፈው ሰው
ዘለዓለሙ አያሰጋው (2x)
አባትዬ የእኔ ወዳጅ (2x)
ኑሮዬ በአንተ እጅ (2x)
አባትዬ የእኔ ከለላ ከለላዬ
በጥላህ ሥር ነው ማደሪያዬ (2x)
በእናቴ ማህፀን ደምሳለ ሆኜ አጥንቶቼም ሳይዋደዱ
አንተው ታውቀው ነበር እንዲህ እንዲሆን የሕይወቴ አካሄዱ
ደግሞ እስከ አሳለፍከኝ በቸርነትህ የትላንቱኑ ጨለማ
ለነገውስ ቢሆን ለምን አላምንም ሕይወቴ በእጅህ ነውና
ተውኩት ሁሉንም ለአንተ ተውኩት
ተይ ነፍሴ እኔ አላውቅም ብዬ እንዳልኩት
ይሁን ያልከው የፀና ለመሆኑ
ምስክር ነው ሰማይ የለም አገር መሆኑ
አዝ፦ የእግዚአብሔር እጅ የያዘው ነገር
እንዳይወድቅ አይፈራ እንዳይጠፋ አይፈራ
ከጥላው ሥር ያረፈው ሰው
ዘለዓለሙ አያሰጋው (2x)
አባትዬ የእኔ ወዳጅ (2x)
ኑሮዬ በአንተ እጅ (2x)
አባትዬ የእኔ ከለላ ከለላዬ
በጥላህ ሥር ነው ማደሪያዬ (2x)
ክብርን የምትገልፅበት ደካማ ሰው ስትፈልግ አገኘኸኝ
እንጂማ በእራሴ እንኳን በአንተ በሰውም ዓይን የማልሞላ ነኝ
ገና በወደድከኝ በንጋት አየሁ ብልስ ምን እልሃለሁ
አንተ ነህ ደጀኔ ተባረክልኝ ከትከሻህ የሚያወርደኝ ማነው
አልጥልሽ አልተውሽ እያልክ
ልፌ ስትደግፈኝ እንደዋልክ
አይቼህ መንፈሴ ረካ
አትተወኝም አትረሳኝም ለካ
አዬ አትረሳኝም ለካ
አትተወኝም በቃ አትረሳኝም በቃ
አሄ አትረሳኝም በቃ
አትተወኝም በቃ አትለቀኝም በቃ
አሄ አትለቀኝም በቃ (2x)