Shewa press


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Новости и СМИ


Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Новости и СМИ
Статистика
Фильтр публикаций


የኢራኑ ፕሬዚዳንት ኢብራሂም ራኢሲ በሄሊኮፕተር አደጋ ህይወታቸው ማለፉ ተገለጸ‼️

የፕሬዚዳንት ኢብራሂም ራኢሲ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ሆሴን አሚር አብዶላሂ በሄሊኮፕተር አደጋ ህይወታቸው ማለፉን ሮይተርስ አስነብቧል፡፡

ፕሬዚዳንቱ ኢራን ከአዘርባጃን ጋር በምትዋሰንበት ድንበር አካባቢ የተገነቡ ሁለት ግድቦችን አስመርቀው ወደ ታብሪዝ እያመሩ ነው አደጋው ያጋጠማቸው፡፡

ሄሊኮፕተሩ ከታብሪዝ ከተማ 50 ኪ.ሜ ርቀት ላይ እክሉ የገጠመው ሲሆን በቦታው የነበረው ጭጋጋማ የአየር ንብረት ለነብስ አድን ቡድኑ አስቸጋሪ እንደነበር ተጠቁሟል፡፡

በዚህም ከፍለጋዎች በኋላ ፕሬዝዳንቱን እና ሚኒስትሩን ያሳፈረው ሄሊኮፕተር ተራራማ እና በረዷማ በሆነው አካባቢ ሲገኝ የእሳት ቃጠሎ ደርሶበት እንደነበርም ነው የተገለፀው፡፡

@showapress


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
አንድ ፋኖ💪
የ አማራ አንገቱ አንድ ነው💚💛❤️

@showapress


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
በአማራ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ የተማረኩ የፌደራል ፖሊስ አባሎች።

@showapresd


ቀይ ቦኔት ሞገሱን አግኝቷል 💪

የ አማራ ፋኖ በጎጃም አድስ ያስመረቃቸው ኮማንዶ ፋኖወች✊

@showapress




ሸዋ የጠላት መጋኛ💪

ለጠላትም ለወዳጅም ይወቁት የሸዋ ፋኖ በቅርብ ቀን በአንድ ዕዝ ይመጣል።

@showapress


የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ ከባለ ቀይ ቦኔቱ የማረከው መሳሪያ💪

@showapress

14.9k 0 10 11 156

Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
በአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ በፕሮፌሰር አስራት ሻለቃና ናደው ሻለቃዎች በጥምረት በተሰራ ልዩ ኦፕሬሽን የተያዘው የደብረብርሃየን ዩንቨርስቲ ፕሬዝዳንት በሸዋ ሸለቆዎች መሃል መግለጫ ሰቷል !! ታላቁን የአማራ ህዝብ ይቅርታ ብሏል !! የነፃነት ታጋዮቹን ፋኖዎች ልባዊ አድንቆትና ምስጋና አድርሷል ።

@Showapress

14.4k 0 43 22 126

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለፋሲካ በዓል በሰላም አደረሳችሁ።

መልካም በዓል‼

@Showapress


Unity is power‼️

@showapress

18k 0 5 5 208

የአማራ ፋኖ ወሎ ዕዝ ዋና አዛዡን ዋርካው ምሬ ወዳጆን አድርጎ መረጠ‼️

በዛሬው ዕለት ሚያዚያ 20 ቀን 2016 ዓ.ም የምስራቅ አማራ ፋኖ እና የወሎ ዕዝ ፋኖ ውህደት ፈጽሟል።

ውህደቱ ከተፈፀመ በኋላ የአማራ ፋኖ ወሎ ዕዝ ዋና አዛዡን ዋርካው ምሬ ወዳጆን፣ ምክትል አዛዡን ደግሞ ኮረኔል ፈንታሁን ሙሃቤን አድርጎ መርጧል።

ከወራት በፊት የተጀመረውና ሚያዚያ 19 ቀን 2016 ዓ.ም ውህደቱን ለመፈፀም የተጀመረው ንግግር በዛሬው ዕለት ሚያዝያ 20 ቀን 2016 ዓ.ም ውህደት በመፈፀም፤ ቀሪ የዕዙን መዋቅራዊ አደረጃጀት በቀጣይ በጋራ ለመሥራት ስምምነት ላይ ተደርሷል።

@showapress


ወሎ ቤተ _አማራ ፋኖ✊💚💛❤️

የአማራ ፋኖ ወሎ ዕዝ እንደሌሎቹ የፋኖ ዕዞች ባስቸኳይ ዕርዳታ ይደረግለት!!

@showapress


"ጥፋት እንጅ ክህደት በአማራ ህዝብ ላይ አንፈጽምም"።

ምስራቅ አማራ ፋኖ ዕዝ
17/08/2016

ከሃያ አምስት በላይ የአድማ ብትና አባላት የምስራቅ አማራ ፋኖ ዕዝ አሳምነው ጽጌ ክፍለ ጦርን ተቀላቅለዋል።ከተቀላቀሉ በኋላም እኛ እውነት ነው አማራ ህዝብ ዘንድ ጥፋት አጥፍተናል ነገር ግን ክህደት አልፈጸምንም።

ከነገ ዛሬ ይለውጣል ብለን በተለይ የአማራ የወሰን ጥያቄዎችን ያስከብራል ብሎም ከአማራ ህዝብ ጎን ይቆማል ያለው የብልጽግና አመራር ራሱን ለሆዱ ሽቶ መሬቱም ለዳግም ወረራ ዳርጎ የአማራን ህዝብ ዳግም ለባርነት አሳልፎ ሊሰጥ እንደሆነ ዘግይተን ብንረዳም ዛሬ ግን ከተከበረው የአማራ ፋኖ ጋር ተቀላቅለናል።

ወደፊትም የትኛውንም ግዳጅ ለመወጣት ዝግጁ መሆናችንን መላው የአማራ ህዝብ ሊረዳልን ይገባል ብለዋል።
በተደጋጋሚ የወራሪው ስርአት ዙፋን ጠባቂዎችም ከቀን ወደ ቀን ወደ ፋኖ እየተቀላቀሉና ግዳጅ እየፈጸሙ ይገኛሉ።

በደቡብ ወሎና በሰሜን ወሎ ዞን የሚንቀሳቀሰው የምስራቅ አማራ ፋኖ ዕዝ ከሁሉም በተለዬ መልኩ የአንድነቱን ጉዳይ አበክሮ እየሰራና ጥሩ ሂደት ላይ መሆኑን አብክሮ መግለጽ ይፈልጋል።

ጓዶች የሞቱለትን አላማ ከግብ እናደርሳለን!!

ምስራቅ አማራ ፋኖ👇👇

https://youtu.be/AItIJCPUYwI?si=-NzWIat-wl396mJi


የአማራ ፋኖ በጎንደር ወደ አንድ አደረጃጀት መጥቷል‼️

የአማራ ፋኖ በጎንደር እና የጎንደር እዝ ወደ አንድ በመምጣት አብረው ለመስራት ወስነዋል።

@showapress


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
በሸዋ የባህር ሃይል ጦርነት ✊
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ነበልባሎች ሻወር እያሰወሰዱት ነው😂

@Showapress


#ይቅርታ❗

ምክትል ሳጂን ታመነ ዱባለ "ያደኩበት ቤተክርስትያን ተገንብቶ በማለቁ የተሰማኝ ደስታን ለመግለፅ ሀላፊዎችን አስፈቅጄ ነው ጥይት የተኮስኩት በዚህም ያስከፋዋችሁ ካለ ይቅርታ አድርጉልኝ" ብሏል።

@Showapress


አርቲስት አማኑኤል ለጥያቄ ትፈለጋለህ ተብሎ ከኤርፖርት በፖሊስ ተይዞ ወደ አዲስ አበባ ፖሊስ ጣቢያ ተወስዷል::

አርቲስት አማኑኤል የአንድ ሰው ትያትር የሆነውን “ ዕብደት በህብረትን “ ቲያትር ለማሳያት ከአዲስ አበባ ወደ እስራኤል ሀገር ሊሄድ ሲል ከአዲስ አበባ ኤርፖርት ለጥያቄ ትፈለጋለህ ብለው ፖሊሶች ይዘውት ወደ አዲስ አበባ ፖሊስ ጣቢያ ይዘውት መሄዳቸው ተሰምቷል።

@showapress


#ጎጃም

ከባህርዳር አንድ ሻምበል የአድማ ብተና አባላት ከነሙሉ ትጥቃቸው የአማራ ፋኖ በ ጎጃም የጣናው መብርቅ ብርጌድን መቀላቀላቸው ተሰምቷል።

@showapress


የአየር ሀይል አዛዥ የጀኔራል ይልማ መርዳሳ ታናሽ ወንድም እና አጎቱ በሸኔ መገደላቸው ተሰምቷል። በርካታ የቤተሰቡ አባላትም በታጣቂ ቡድኑ መታገታቸው ተሰምቷል።

@showapress


#ራያ‼️

ከአላማጣ እና አካባቢው 29 ሺህ ህዝብ መፈናቀሉ ተገለጸ‼️
ተፈናቃዮቹ በቆቦ፣ወልዲያ እና ሰቆጣ ከተሞች መጠለላቸው ተገልጿል።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ባወጣው ሪፖርት 29 ሺህ ዜጎች ከራያ እና አላማጣ አካባቢዎች መፈናቀላቸውን አስታውቋል፡፡

እንደ ድርጅቱ ሪፖርት ከሆነ ከሰሞኑ በትግራይ እና አማራ ክልል አዋሳኝ ቦታዎች ላይ ባገረሸው ግጭት ምክንያት ዜጎች ከመኖሪያ ቤታቸው ተፈናቅለዋል ብሏል፡፡

ተፈናቃዮቹ በቆቦ፣ወልዲያ እና ሰቆጣ ከተማ በሚገኙ መጠለያዎች ላይ እንደተጠለሉም ድርጅቱ አስታውቋል፡፡
በአካባቢው ባለው አለመረጋጋት ምክንያት ተጨማሪ ዜጎች ሊፈናቀሉ እንደሚችሉ የገለጸው ድርጅቱ ለተፈናቃዮች ውሃ፣ ምግብ እና ሌሎች ህይወት ማቆያ ድጋፍ በማድረግ ላይ መሆኑንም ገልጿል፡፡

አሁን ላይ ከለጋሽ ተቋማት እና ሀገራት የሚገኘው ድጋፍ እየተሟጠጠ በመሆኑ በአካባቢው ያለው ማህበረሰብ የሚችለውን ድጋፍ እያደረገ እንደሆነም ተገልጿል፡፡

ለተፈናቃዮቹ መጠለያ፣ የሕክምና አገልግሎት እና ሌሎች መሰረታዊ ድጋፎችን ማድረግ ይገባል ያለው ድርጅቱ የኢትዮጵያ አደጋ መከላከል እና ዝግጁነት ኮሚሽን ሰራተኞች ወደ ስፍራው ተሰማርተዋልም ተብሏል፡፡

ተፈናቃዮቹ ከአንድ ሳምንት በፊት በሚኖሩባቸው አካባቢዎች የህወሃት ታጣቂዎች ወደ ራያ እና አላማጣ አካባቢዎች መምጣታቸውን ተከትሎ ቤታቸውን ጥለው ለመሰደድ እንደተገደዱ ተገልጿል፡፡

ከተፈናቀሉት 29 ሺህ ዜጎች ውስጥ 70 በመቶዎቹ ህጻናት እና ሴቶች ሲሆኑ ቀሪዎቹ አዛውንቶች እና ታዳጊዎች ናቸው ተብሏል፡፡

@Showapress

Показано 20 последних публикаций.