The ጀማል (ዘ ጀማል )


Гео и язык канала: Эфиопия, Английский
Категория: Новости и СМИ


🏇 ይህ #the_ጀማል የቴሌግራም ገፅ ነው !
=> በቻናሉ
📌 ፈጣን ፥
📌 ትኩስ ፥
📌 ወቅታዊ እና
📌 አዳዲስ መረጃዎች እንደወረዱ በቅፅበት ፥ በትኩሱ ይደርሳችኋል ! ከዓለም 👊
👊 ይወዳጁን ፤ በእርግጥም ይወዱታል !

Связанные каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Английский
Категория
Новости и СМИ
Статистика
Фильтр публикаций


መደበኛ ሎተሪ 1736ኛ ዕጣ ትናንትና   ሚያዝያ 16 ቀን 2017 ዓ.ም በኢትዮጵያ ሎተሪ  አገልግሎት በዕድል አዳራሽ የወጣ ሲሆን የወጡት የዕጣ ቁጥሮችም ከዚህ ጋር ተያይዟል።
1 ዕጣ  114738 👉600,000ብር
2 ዕጣ 064567 👉200,000ብር
3 ዕጣ 037570 👉100,000ብር
4 ዕጣ 007784 👉50,000ብር


ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ለመከታተል የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
https://t.me/thejamalnews
#the_ጀማል


መደበኛ ሎተሪ 1736ኛ ዕጣ ትናንትና   ሚያዝያ 16 ቀን 2017 ዓ.ም በኢትዮጵያ ሎተሪ  አገልግሎት በዕድል አዳራሽ የወጣ ሲሆን የወጡት የዕጣ ቁጥሮችም ከዚህ ጋር ተያይዟል።
1 ዕጣ  114738 👉600,000ብር
2 ዕጣ 064567 👉200,000ብር
3 ዕጣ 037570 👉100,000ብር
4 ዕጣ 007784 👉50,000ብር


የስቅለት በዓል በመላ የክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ እየተከበረ ይገኛል።

እንኳን ለስቅለት በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ለመከታተል የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
https://t.me/thejamalnews
#the_ጀማል


የቀድሞው ፕሬዚዳንት መንግሥቱ ኃይለማርያም አውሮፕላን ተጠግኖ ዳግም ለአገልግሎት መብቃቱ ዛሬ ተነግሯል።

አውሮፕላኑን ከ37 ዓመት በኋላ የበረራ አገልግሎት እንዲሠጥ ማድረግ መቻሉን የመከላከያ ሠራዊት ገልጿል።
ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ለመከታተል የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
https://t.me/thejamalnews
#the_ጀማል


በአደገኛ የትራፊክ አደጋ ዛሬም የአንድ ሰው ሕይወት ተቀጥፏል።

#Ethiopia | በዳሞት ወይዴ ወረዳ ብልቦ በዴሳ ት/ቤት በራፊ የዱጉና ፋንጎ ወረዳ አምቡላንስ ከወላይታ ሶዶ አትክልት ጭኖ ከሚመጣው ዳማስ ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨቱ፣ በዳማስ መኪና ውስጥ የነበረች የበዴሳ ከተማ አትክልት ነጋዴ የሆነች እህታችን በአደጋው ሕይወቷ ተቀጥፏል።

በአምቡላንሷ ውስጥ የሚገኙ የጤና ባለሙያዎች መጠነኛ ጉዳት የደረሳቸው ሲሆን ከባድ ጉዳት የደረሰበት የዳማስ ሾፌርን ጨምሮ 5 ሰው ወደ ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለአፍተኛ ሕክምና ክትትል ተልከዋል።

የዱጉና ፋንጎ ወረዳ ጤና ባለሙያ ጓደኛዬ ኤፍሬም ታዴዎስ ኮሽሞ እና ጓደኞቹ በፈጣሪ ዕርታ በሕይወት ተርፈዋል።

ከወላይታ ሶዶ ወደ ሐዋሳ የሚዘልቀው መንገድ ደህንነቱን ለማስጠበቅ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ባለበት ወቅት፣ የአደጋ ጠቋሚ Information Board ከተሰቀለበት ት/ቤት በራፊ በ50 ሜትር ርቀት የዛሬው አደጋ መከሰቱ እጅግ አሳዛኝ ነው።

አሽከርካሪዎች በፈጣሪ ስም እንለምናችሁ ተረጋግታችሁ፣ የመንገድ ዳር ምልክቶችንና ኢንፎርሜሽን ቦርድ ላይ የተገለጸውን መልዕክት በመመልከትና በመተግበር አሽከርክሩ።

ፈጣሪ የሟች እህታችንን ነፍስ ይማር፤
ለቤተሰቦቿ መጽናናትን ያድልልን።
ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ለመከታተል የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
https://t.me/thejamalnews
#the_ጀማል


ሰበር ዜናዎች
ሚያዝያ 8/2017

👉በትግራይ ክልል በተፈጠረው የፓለቲካ  አለመግባባት ምክንያት ወደ ክልሉ ቤንዚን(ነዳጅ ) መጋባት መቆሙን ተሰምቷል እንደ መረጃዎች ከሆነም ከጦርነቱ  ቀደም ብሎ በቀን ከ8 እሰከ 16 ቦቴ እንደምገባ ነው የተገለፀው ።
👉የደቡብ ክልል መንግስት የትንሣኤ በዓል በማስመልከት ለ9መቶ 90 (990) የህግ ታራሚዎች ይቅርታ መድረጉን ተሰምቷል ።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር  ጥላሁን ከበደ እንደገለጹት ከሆነ በማረሚያ ቤት መልካም ስነምግባር ያሳዩት መሆናቸውን ፀደቀ ያገኘው መረጃ ያመልክታል ።
👉በእስር ቤት  የሚገኙት ቲክቶከር ጆን ዳንኤል እና ናዮ( ዪዲዲያ) ትናትና ሚያዝያ 7 ቀን የፍርድ ቤት ቀጠሮ ነበራቸው የናዮ የመውለጃ ጊዜዋ መድረሱን ተከትሎ ልጄን ለመውለድም ጋንዲ ሆስፒታል ይፈቀድልኝ ብላ መጠየቃን የተሰማ ቢሆንም ፍርድ ቤቱ ጉዱዩ ከመረመረ በውላ
ባለችበት እስር ቤት (ቃሊት እስርቤት) እንድትወልድ ፍርድ ቤት ወስኗል ተብሏል።
👉በኤርትራ የምገኘውን ኤንባሲውን አሜሪካ ልትዘጋ መሆኑን ተሰምቷል እንደ መረጃዎች ከሆነ የኤርትራን ጨምረው 10 ኤምባሲዎችን ልትዘጋ ፖለቲኮ አስነብቧል ።ፖለቲኮ እንደዘገበው የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የወጪ ቅነሳ አዲስ እቅድ አውጥቷል፡፡ በዚህ እቅድ መሰረት የመስሪያ ቤቱን አመታዊ ወጪ በሀምሳ ፐርሰንት ለመቀነስ፣ መታሰቡን አስታውቋል እቅዱን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችሉ ምክረ ሀሳቦች መቅረባቸውን ፀደቀ ተማልክቷችል።



👉ዜና ውይም ማስታወቂያ  እንዲፃፍላቸው  ለ 1facebook  2 tik tok  3 telegram  እና  ለመሳሰሉት በቅናሽ ና በተመጣጣኝ ዋጋ እየፃፍን እናስረክባለን በፍጥነት ። 

ለበለጠ መረጃ  👉0937436816 ይጠይቁን
# tsedekenews
ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ለመከታተል የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
https://t.me/thejamalnews
#the_ጀማል


የሚያዝያ 7 ቀን 2017 የዓለም ዜና
• በአማራ ክልል ከመንግሥት የሚዋጉ ታጣቂ ኃይሎች “ችግሮችን ለመፍታት ወደ ውይይት እንዲመጡ” የአማራ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ጥሪ አቀረበ። ምክር ቤቱ ጥሪውን ያቀረበው የመንግሥት የጸጥታ አስከባሪዎች ከፋኖ ታጣቂዎች የሚያደርጉት ውጊያ ሁለተኛ ዓመቱን ሊደፍን በተቃረበበት ወቅት ነው።
• በደቡብ ሱዳን እየተባባሰ በመጣው ግጭት ካለፈው መጋቢት ወዲህ ከ200 በላይ ሰዎች መገደላቸውን እና ከ125,000 በላይ የሚገመቱ ሰዎች መፈናቀላቸውን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አስታወቀ። ድርጅቱ ዛሬ ማክሰኞ ባሰራጨው መግለጫ ከአየር በተፈጸመ ድብደባ ብቻ ከ180 በላይ ሰዎች መገደላቸውን፤ ከ250 በላይ መቁሰላቸውን ይፋ አድርጓል።
• ሶማሊያ ከ56 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ለምርጫ ድምጽ ሰጪዎችን መመዝገብ ጀመረች። ዛሬ የተጀመረው የድምጽ ሰጪዎች ምዝገባ መንግሥታት የሚያወጧቸውን ሕግጋት የሚያሟሉ ዜጎችን የመምረጥ መብት ወደሚያረጋግጥ ዓለም አቀፍ አሠራር ሶማሊያን አንድ እርምጃ የሚያቀርብ ነው።
• በሱዳን አስገድዶ መድፈር እንደ ጦር ሥልት ጥቅም ላይ እየዋለ እንደሚገኝ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አስጠነቀቀ። ዛሬ ሁለተኛ ዓመቱን የደፈነው የሱዳን ጦርነት እንዲቆም የአፍሪካ ኅብረትን ጨምሮ የዓለም ሀገራት ጥሪ አስተላልፈዋል።
• እስራኤል በጋዛ ሠርጥ በሚገኘው የኩዌት የመስክ ሆፒታል ደጃፍ በፈጸመችው የአየር ጥቃት አንድ የሕክምና ባለሙያ ሲገደሉ በርካቶች ቆሰሉ። ጥቃቱ የተፈጸመው በመቶ ሺሕዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በተበታተኑ የድንኳን መጠለያዎች በሚኖሩበት ሙዋሲ የተባለ አካባቢ ነው።
• አልጄሪያ አስራ ሁለት የፈረንሳይ ዲፕሎማቶች ለማባረር ያሳለፈችው ውሳኔ መዘዝ እንደሚኖረው የፈረንሳይ ውጪ ጉዳይ መሥሪያ ቤት አስጠነቀቀ። እርምጃውን "አሳዛኝ" ያሉት የፈረንሳይ ውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ዦን ንዌል ባሮ ሀገራቸው የአልጄሪያን ውሳኔ በዝምታ እንደማታልፍ ዛሬ ማክሰኞ ተናግረዋል።

ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ለመከታተል የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
https://t.me/thejamalnews
#the_ጀማል


# tsedekenews //ሚያዝያ 5/2017ጠዋት ዓላም በፀደቀ እይታ ዜናዎች
# tsedekenews //መንግሥት የሰብዓዊ ዕርዳታ ፈላጊዎችን ቁጥር 86 በመቶ ቀንሻለሁ ብሏል
በየዓመቱ ከውጭ ይመጣ የነበረ አንድ ቢሊዮን ዶላር ማዳኑንም ገልጿል።
ባለፉት አምስት ዓመታት በኢትዮጵያ የሰብዓዊ ዕርዳታ ፈላጊዎችን ቁጥር በ86 በመቶ መቀነሱን፣ የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አስታወቀ፡፡የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከኮሚሽኑ የሥራ ኃላፊዎች ጋር፣ በኢትዮጵያ አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ረቂቅ አዋጅ  ላይ የአስረጂና የባለድርሻ አካላት መድረክ ውይይት ሲደረግ ነው ይህ የተገለጸው፡፡ረቂቁን በተመለከተ ማብራሪያ የሰጡት ኮሚሽነር ሽፈራው ተክለ ማሪያም (አምባሳደር)፣ ‹‹ባለፉት አምስት ዓመታት ጨዋታ ቀያሪ የሆነ ወረቶችን ማስመዝገብ ችለናል፤›› ካሉ በኋላ፣ ‹‹በትልቅ ስኬትነት የምናቀርበው ባለፉት አምስት ዓመታት የሰብዓዊ ዕርዳታ ፈላጊዎችን ቁጥር እስከ 86 በመቶ የቀነሰበት
ነባራዊ ሁኔታ መፈጠሩን ነው፤›› ብለዋል፡፡፡(ራፖርተር ዘግቧል )

# tsedekenews //የወንድ የዘር ፍሬ የሩጫ  ውድድር በአሜሪካ ሊካሄድ ነው ተባለ
ለመጀመሪያ ጊዜ የወንድ የዘር ፍሬ ውድድር ግንቦት 2 በካሊፎርኒያ የሚካሄድ ሲሆን፣ ከሁለት ዩኒቨርሲቲዎች ማለትም ከዩኤስሲ እና ከዩሲኤልኤ የተወሰዱ ናሙናዎች በአጉሊ መነጽር በሚታይ የመሮጫ ላይ ውድድር  ይወዳደራሉ።
ዝግጅቱ በሆሊውድ ፓላዲየም ፊት ለፊት 5,000 ተመልካቾች በተገኙበት የሚካሄድ ሲሆን፣ የቀጥታ ስርጭት፣ ተንታኞች እና ውርርድም ይኖራል ተብሏል።

# tsedekenews //የሆሳዕና በዓል በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን አማኞች ዘንድ እየተከበረ ነውየሆሳዕና በዓል በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን አማኞች ዘንድ በዛሬው ዕለት እየተከበረ ይገኛል።በዓሉ በአዲስ አበባ ቅድስት ልደታ ማርያም ካቴድራል የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ ካርዲናል ብርሃነ ኢየሱስ ሱራፌል በተገኙበት በተለያዩ ስነስርዓቶች ተከናውኗል፡፡የሆሳዕና በዓል ኢየሱስ ክርስቶስ በአህያ ጀርባ ተቀምጦ ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ በተለይም አረጋውያን፣ ሴቶች፣ ወንዶች፣  ወጣቶች እና ሕጻናት “ሆሳዕና ለዳዊት ልጅ፣ ሆሳዕና በዓርያም” በማለት በክብር መቀበላቸው የሚታወስበት በዓል ነው፡፡

# tsedekenews//አሜሪካ በአንዳንድ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች ላይ የጣለችው አዲስ ታሪፍ የተወሰኑ ምርቶችን እንደማያካትት ተረጋገጠ

[#tsedekenews ]ሲኤንቢሲ ኒውስ እንደዘገበው ወደ አሜሪካ የሚገቡ እንደ ስማርት ስልኮች፣ ኮምፒውተሮችና የመሳሰሉት በርካታ የኤሌክትሮኒክስ መሣሪያዎች በቅርቡ በአሜሪካ መንግስት በታወጀው አዲስ የገቢ ቀረጥ እንደማይጎዱ ተረጋግጧል።
ይህ ዜና እነዚህን ምርቶች ከአስመጪ ሀገራት ወደ አሜሪካ ለሚያቀርቡ ኩባንያዎች እንዲሁም በአሜሪካ ውስጥ ላሉ ሸማቾች እፎይታን የሚሰጥ ነው። መንግስት ይህንን ውሳኔ ያደረገበት ምክንያት እስካሁን በግልጽ ባይገለጽም፣ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች በዘመናዊው ህይወት ውስጥ ያላቸውን ወሳኝ ሚናና በዋጋቸው ላይ ሊኖር የሚችለውን አሉታዊ ተፅዕኖ ከግምት ውስጥ ያስገባ ሳይሆን አይቀርም።
# tsedekenews
ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ለመከታተል የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
https://t.me/thejamalnews
#the_ጀማል


የተባረክ መስጂድ አጥር በሌሊት በጸጥታ ሀይሎች እንዲፈርስ መደረጉን የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት አሳወቀ

በአዲስ አበባ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ሜክሲኮ አካባቢ ወረዳ 10 ተባረክ (ጀርመን) መስጂድ ህጋዊ ካርታ ያለው እና ከ1967 ጀምሮ ሲሰገድበት የቆየ መስጅድ መሆኑን አዲስ አበባ መጅሊስ ገልጿል።

አካባቢውን በአዲስ መልክ ለማልማት መንግስት የጀመረውን እንቅስቃሴ በመደገፍ እና መስጅዱን በአዲስ መልክ ለመስራት ፕሮጀክት ተዘጋጅቶ ለሚመለከተው የመንግስት ተቋም ገቢ ተደርጎ ክትትል እየተደረገ ባለበት ወቅት አካባቢውን እያለማ የሚገኘው ኢግልስ ሂል የፌደራል የሜጋ ፕሮጀክት ተወካዮች፣ የወረዳ እና ክ/ከተማ የመንግሥት አመራሮች በተገኙበት የመስጅዱን ዙሪያ በማጠር እና በሰላማዊ መንገድ ለአካባቢው ጀመዓ በማስረከብ መስጅዱ እየተሰገደበት ይገኛል።

የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት ከከተማ መስተዳድሩ የሰላም እና ጸጥታ ቢሮ አስተዳደር ጋር በጉዳዩ ላይ ሰፊ ውይይት ያደረገ ሲሆን አጥሩ ባለበት ሁኔታ በውይይት ዘላቂ መፍትሄ እንዲሰጥ ከስምምነት ተደርሶ ነበር። ከዚህም በተጨማሪ ረመዳን 28 የአካባቢው ጀመዓ ባዘጋጀው የኢፍጣር ፕሮግራም ላይ የክ/ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶክተር አዲሱ ሻንቆ በአካል በመገኘት የማህበረሰቡን ጥያቄ ለመመለስ እየሰሩ መሆኑን አሳውቀዋል።

ይህ በእንዲህ እያለ በሰላማዊ መንገድ በቀን የተገነባውን የመስጅድ አጥር ጨለማን ተገን አድርጎ ማፍረስ እና በመስጅዱ ውስጥ የሚገኙ የመስጅድ ኻዲሞችን ማሰር በምንም መመዘኛ ህግ ማስከበር ሊሆን እንደማይችል አዲስ አበባ መጅሊስ አስታውቋል።

በመሆኑም ከፍተኛ ም/ቤቱ ድርጊቱን አጥብቆ ያወግዛል። በመጨረሻም የፌደራል የሜጋ ፕሮጀክት ተወካዮች እና የመንግስት የስራ ሀላፊዎች ባሉበት የተገነባው የመስጅድ አጥር ወደ ነበረበት እንዲመለስ እና ያለምንም ጥፋት ከመስጅድ የታሰሩት ሰዎች በአስቸኳይ እንዲለቀቁ እናሳስባለን ሲል መጅሊሱ በማህበራዊ ትስስር ገፁ አስታውቋል።

Via ሀሩን ሚዲያ

ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ለመከታተል የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
https://t.me/thejamalnews
#the_ጀማል




ፈረስና በግ ያለው ገበሬ ፈረሱ በጠና ታመመበት። በአካባቢው የሚገኝ የእንሰሳት ሃኪም ተጠርቶ ፈረሱን አየውና "ይህ ፈረስ በጠና ታሟል። ለ3 ቀን የሚሆን መድሃኒት እሰጠዋለሁ። በ3 ቀን ውስጥ ካልተሻለው በሽታው ወደ ሌሎች ፈረሶች ሳይተላለፍ በፊት እንገድለዋለን" አለ።

ይህንን የሰማው በአካባቢው የነበረው በግ ወደ ፈረሱ ሄዶ "በ3 ቀን ውስጥ ከህመምህ ካልተሻለህ ሰዎቹ ይገድሉሃልና በርታ በርታ በል" ሲል ነገረው።

በመጀመሪያው ቀን ሃኪሙ ለፈረሱ መድኃኒቱን ሰጥቶት እንደሄደ በጉ ወደ ፈረሱ መጣና "አሁን ለመነሳት ሞክር። አይዞህ ተነስ ፣ ተነስ፣ አለበለዚያ ይገድሉሃል" እያለ አበረታታው።

በሁለተኛው ቀን ሃኪሙ መድኃኒቱን ሰጥቶት እንደሄደ በጉ መጣና "ዛሬ ሁለተኛ ቀንህ ነው። ቀስ እያልክ ተነስ። አዎ! በርታ ተነስ። ትንሽ ቀርቶሃል" እያለ አበረታታው።

በ3ኛው ቀን ሃኪሙ መድኃኒቱን ሰጥቶት ሲወጣ በጉ ወደ ፈረሱ መጥቶ "ዛሬ የመጨረሻ ቀንህ ነው። ካልተሻለህ ይገድሉሃል። አዎ! ግድግዳውን ተደግፈህ ቁም። አዎ! አሁን ቀስ እያልክ ተራመድ። አዎ! በርታ! ፍጥነት ጨምር።  ሩጥ! ሩጥ! ሩጥ!

የፈረሱ ባለቤት የሚጋልብ ፈረስ ድምፅ ሰምቶ ሲወጣ ፈረሱ ድኖ ሲቦርቅ አየውና በደስታ እያጨበጨበ እንዲህ ሲል ለቤተሰቦቹ ትዕዛዝ ሰጠ "ፈረሴ ከህመሙ ዳነልኝ! በጣም ተደስቻለሁ። ዛሬ በቤታችን ትልቅ ግብዣ ይደረጋል። ማነህ! የደስ ደስ በጉን አውጣና እረድልኝ"

ወንድሜ ! እንግዲህ ምን እልሃለሁ? ምስኪኑ በግ ማለቴ  መልካም ባደረግን እንድንታረድ መታሰቡ አይገርምም? አንተም ለራስህ ስትል ከመጣል ለመትረፍ ነቃ ብለህ ተራመድ።

ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ለመከታተል የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
https://t.me/thejamalnews
#the_ጀማል


የስራስር ልማት አብዮት በሁልባራግ ወረዳ ተቀጣጥሎ ቀጥሏል።
መጋቢት 23/7/2017
ኬራቴ
በስልጤ ዞን በሁልባራግ ወረዳ ከዚህ ቀደም ለምግብነት ይውሉ ያልነበሩ ግን ደግሞ ከፍተኛ የሆነ ለሰው ልጅ ተስማሚ ንጥረ ነገሮችን የያዙ ለምግብ ዋስትናችን ወሳኝ የሆኑ የስራ ስር ሰብሎችን የማላመድና የማልማት እንቅስቃሴ የተጀመረ ሲሆን በዛሬው እለትም ከ15000 በላይ የብርትኳናማ ስኳር ድንች ቁርጥራጭ ከምስራቅ ጉራጌ ሶዶ ወረዳ ማስመጣት የተቻለ ሲሆን በቀጣይ ጊዜያት ሌሎች የስራስር አይነቶችን በስፋት የማልማት ስራው ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል።


እንኳን ለ 1446 የኢድ አልፈጥር በዓል አደረሳችሁ!

ኢድ ሙባረክ!
ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ለመከታተል የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
https://t.me/thejamalnews
#the_ጀማል


በማይናማር የመሬት መንቀጥቀጥ የሞቱት ሰዎች ቁጥር ከ1,600  በላይ ደርሷል ከ3,400 በላይ ሰዎች ተጎድተዋል ሲሉ የሀገሪቱ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ለመከታተል የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
https://t.me/thejamalnews
#the_ጀማል


እዩ ጩፋ እንዲህ ብሏል፡ - "በመጀመሪያ የመንግስት ፓትሮል የሚወጣው ዌልካም ለማለት የሚወጣውን የህዝብን ደህንነት ለመጠበቅ ነው ይህ የመንግስት ተቀዳሚ ሃላፊነት ነው በመቀጠል አምላክ የላከው አገልጋይ ወደ ከተማ ሲገባ ዌልካም ለማለት ነው የሚወጣው።  ከዚህ በኋላ ቪ8 ቶች (መኪኖች) ቪ8 ቶች ብቻ አይደለም በዚህ ዘመን የተፈጠረም ነገር ካለ ተጨምሮ አገልጋዮች ዌልካም ይባላሉ።  ለመቀበል እንደምትቸገሩ አውቃለሁ ነገር ግን ምርጫ የላችሁም አገልጋዮችን በንቀት አትዩ።  አገልጋዮች የእግዚአብሔር ድምጽ ፣ቃል አቀባዮች እና ምልክቶች ናቸው።

"በማስፈራራት እና በማስጨነቅ ቀጥሎ የሚነሳውን ትውልድ ተስፋ ለማስቆረጥ የምትፈልጉ ሰዎች እኔ አለሁ ከዚህም በኋላ ፊት ለፊት ቆሜ ለሚመጣው ትውልድ በር ለመክፈት ከፊት አለሁ።  አንዳንድ ሰዎች ዘመኑ በሚመጥን መልኩ መንቀሳቀስን እንደ ሃጥያት ያያሉ።  ሰባት እና ስምንት ፓትሮል ለምን ይመደባል ?
በዚህ ልክ መታጀቡ ለምን አስፈለገ ? የምትሉ ሰዎች ለአገልጋዮች መንግስታዊ የሆነ ጥበቃ ፣ ከለላ፣ ዌልካም  ያስፈልጋል።

"አንድ በእግዚአብሔር ለተሾመ አገልጋይ ምን ያህል ክብር እንደሚገባ መንግስት እና መንግስታዊ የሆኑ መዋቅሮች በተረዱበት በዚህ ጊዜ የቤተክርስቲያን መሪዎች አይናቸው መከደኑ ከምንም በላይ የሚያስገርም ነው።  ቪ8 በዛ፣ ፓትሮል በዛ የምትሉ ሰዎች እግዚአብሔር ባንተ ኮልኮሌ እንዲታጀብ ነው የምትፈልገው ? እግዚአብሔር በፓትሮል የሚታጀብ አምላክ አይደለም ፓትሮሉም ለኛ ነው እኛ ነን የምንታጀበው ከዚህ በኋላ። ብታምኑም ባታምኑም በኢትዮጵያ ምድር በራሳቸው ጀት እየተንቀሳቀሱ የሚያገለግሉ አደገኛ ሰዎች ይነሳሉ። የምታስተላልፉት መልዕክት ተስፋ ከመቁረጥ የመነጨ ይመስላል። ሀዋሳ ስንገባ የተደረገልን አቀባበል ያስደነገጣችሁ ሰዎች ሰላም ናችሁ ? ለማንኛውም ከዚህ በኋላ በሚደረጉ ክሩሴዶች ከዚህ የበለጠ ነገር እንደሚሆን እንዳትጠራጠሩ ከወዲሁ አረጋግጥላችኋለሁ። የበሻሻው ዐቢይ እና የሾለው ነብይ በተራ ጫጫታ ይጠፋሉ ብሎ ማሰብ ተራ ቅዠት ነው"

#the_ጀማል

ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ለመከታተል የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
https://t.me/thejamalnews
#the_ጀማል




አምስት የኢቢኤስ ቴሌቪዥን ጣቢያ ሰራተኞች “በሽብር ወንጀል” ተጠርጥረው ፍርድ ቤት ቀረቡ

የፌደራል ፖሊስ “በሽብር ወንጀል ጉዳይ” ጠርጥሬያቸዋለሁ ያላቸውን አምስት የኢቢኤስ ቴሌቪዥን ጣቢያ ሰራተኞችን፤ በዛሬው ዕለት ፍርድ ቤት አቀረበ። ጉዳዩ የቀረበለት የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት፤ ፖሊስ በጠየቀው የ14 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ላይ ብይን ለመስጠት ለመጪው ሰኞ ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።

የፌደራል ፖሊስ የጊዜ ቀጠሮውን የጠየቀው፤ በስምንት ተጠርጣሪዎች ላይ እያካሄደ ያለውን የምርመራ ስራ “በሰው እና በሰነድ ማስረጃ በስፋት ለማጣራት” በሚል ነው። ከስምንቱ ተጠርጣሪዎች ውስጥ ባለፈው ሳምንት እሁድ በኢቢኤስ ቴሌቪዥን ጣቢያ በተሰራጨ ዝግጅት ላይ “የሀሰት ታሪኳ” ቀርቧል የተባለው ብርቱካን ተመስገን ትገኝበታለች።


#the_ጀማል

ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ለመከታተል የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
https://t.me/thejamalnews
#the_ጀማል


ፆታን መሠረት ያደረጉ ወንጀሎችን በፍጥነት ለመዳኘት ልዩ ችሎት ሊቋቋም ነው

ፆታን መሠረት ያደረጉ ወንጀሎችን በተፋጠነ ሁኔታ ለመዳኘት የሚያስችል ልዩ ችሎት ለማቋቋም ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ ተገለጸ።

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና "ጀስቲስ ፎር ኦል ፕሪዝን ፌሎውሺፕ ኢትዮጵያ" የተባለ ድርጅት በጋራ ባዘጋጁት ሰነድ ላይ፣ በተለይም በግጭት ወቅት የሚፈፀሙ ፆታን መሰረት ያደረጉ ወንጀሎችን በፍጥነት ወደ ፍርድ ቤት ለማቅረብ የሚያስችል አሰራር ተቀምጧል።

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኛ መላኩ ካሳዬ እንደተናገሩት፣ ይህ ሰነድ በፌዴራል ፍርድ ቤትና በዩኒቨርሲቲዎች በተውጣጡ ባለሙያዎች የተዘጋጀ ሲሆን፣ ለሚመለከተው አካል ቀርቦ ተግባራዊ ለማድረግ በዝግጅት ላይ ነው። ይህንን ሰነድ በተመለከተ መጋቢት 13 እና 14፣ 2017 ዓ.ም. በአዳማ ከተማ ለሚዲያ ባለሙያዎች ስልጠና ተሰጥቷል ሲል ሪፖርተር ፅፏል።

ዘገባው ,ፀ

#the_ጀማል

ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ለመከታተል የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
https://t.me/thejamalnews
#the_ጀማል


የታይዋን ፕሬዚደንት የግል ጠባቂዎች የቻይና ሰላይ ሆነው ተገኙ።

ዘቴሌግራፍ በፊት ገጹ ይዞት በወጣው መረጃ የታይዋኑ ፕሬዝደንት ላይ ቺንግ-ዶ አራት የግል ጠባቂዎች የቻይና ሰላይ ሆነው በመገኘታቸው በቁጥጥር ስር ውለዋል።

አራቱ የፕሬዝዳንቱ የግል ጠባቂዎች ሚስጥራዊ መረጃዎችን ለቻይና አሳልፈው በመስጠት የተወነጀሉ ሲሆን ከ10 ወር ጀምሮ እንደየጥፋታቸው ክብደት እስከ ሰባት ዓመት በሚደርስ እስራት መቀጣታቸውም ተነግሯል።

ውጥረት ተለይቶት በማያውቀው የቻይና እና ታይዋን ግንኙነት የስለላ ዜና አዲስ ነገር ባይሆንም ይህኛው ክስተት ግን ትንሺቱን ደሴት ከዳር ዳር ከማሸበር ባለፈ የተቀረውን ዓለም ጭምር እጅን በአፍ ያስጫነ ሆኗል።

ዘገባው m

#the_ጀማል

ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ለመከታተል የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
https://t.me/thejamalnews
#the_ጀማል


➜"ኢቢኤስ ላይ ያቀረብኩት ትውና ነበር"  ብርቱካን ተመስገን
''እናትና አባት አለኝ ''
"ያገባው የተዳርኩ ተከብሬ ልጅ የወልድኩ ነኝ ኢቢኤስ ላይ ያቀረብኩት ትውና ነበር ልጅ የወልድኩት ከባሌ ነው ፣ እንጂ እንዳልኩት ተደፍሬ አይደለም።"


''ቤቷ ሙሉ ነው ''
ቤተሰቦቿም ደህና ናቸው በገንዘብ  የደህና ቤተሰብ ልጅ ናት
እስከዚህ ድረስ ልመና የሚስወጣት ነገር የለም''
በዚህ አጋጣሚ ግን የኢትዮጵያን ህዝብ ይቅርታ እንጠይቃን


ብርቱካን 👇

''ልብ ህመም አለብኝ ግን እግዚአብሔር ይመስገን ጤነኛ ነኝ ''
ነፍሰጡር ሁኜ ነው የተጋባንው ከእሱ ውጭ ሌላ አላቅም

የብርቱካን ባል ንግግር 👇
      ''ትዳር መስርተናል ''
        ''የተጋባንው ስርዓት ነው''

ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ለመከታተል የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
https://t.me/thejamalnews
#the_ጀማል

Показано 20 последних публикаций.