#Update
የቀድሞዉ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ከቀረበባቸው ሁለት ክሶች ነፃ ቢሆኑም የሀዋሳ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀሪ መዝገቦች አሉባቸው።
የቀድሞው የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ረ/ፕሮፈሰር ፀጋዬ ቱኬ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ከተመሰረተባቸው ሁለት ክሶች ነፃ መባላቸዉን መዘገባችን አይዘነጋም።
ነገርግን የቀድሞ ከንቲባ በሀዋሳ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀሪ አራት ክሶች እንዳሉባቸዉና ፍርድ ቤቱ ለዉሳኔ ቀነ ቀጠሮ መስጠቱን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለጠበቆች አረጋግጧል።
በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የነበራቸዉን ሁለት የክስ መዝገቦች አስመልክቶ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃ ያደረሱት ጠበቃቸው አቶ ገብረመድህን ተክላይ " አንድ ዓመት ሙሉ ስንከታተል የነበረው የሙስና (ወይንም) ጉቦ የመቀበል ወንጀል እና በሕገወጥ መንገድ የተገኘን ገንዘብ ሕጋዊ አስመስሎ የመጠቀም ወንጀል " በሚል ቀርቦባቸዉ ከነበረዉን ክስ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሀዋሳና አከባቢዋ ምድብ ችሎት ዛሬ ሙሉ በሙሉ በነፃ አሰናብቷቸዋል።
በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ ፍርድ ቤት ደግሞ ቀሪ የክስ መዝገቦች እንዳሏቸዉ የጠቀሱት ጠበቃቸው አቶ ገብረመድህን ተክላይ እሳቸዉ ግን ጥብቅናቸዉ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ለነበራቸው ሁለቱ መዝገቦች ብቻ መሆኑን ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በጊዜ ቀጠሮ ላይ ባሉ መዝገቦች ዙሪያ ጉዳዩን ከያዙ ጠበቆች ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ያደረገዉ ሙከራ ለጊዜዉ አልተሳካም።
መረጃዎችን እንዳገኘን ተጨማሪ ዘገባ የምናደርስ ይሆናል።
@tikvahethiopia
የቀድሞዉ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ከቀረበባቸው ሁለት ክሶች ነፃ ቢሆኑም የሀዋሳ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀሪ መዝገቦች አሉባቸው።
የቀድሞው የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ረ/ፕሮፈሰር ፀጋዬ ቱኬ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ከተመሰረተባቸው ሁለት ክሶች ነፃ መባላቸዉን መዘገባችን አይዘነጋም።
ነገርግን የቀድሞ ከንቲባ በሀዋሳ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀሪ አራት ክሶች እንዳሉባቸዉና ፍርድ ቤቱ ለዉሳኔ ቀነ ቀጠሮ መስጠቱን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለጠበቆች አረጋግጧል።
በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የነበራቸዉን ሁለት የክስ መዝገቦች አስመልክቶ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃ ያደረሱት ጠበቃቸው አቶ ገብረመድህን ተክላይ " አንድ ዓመት ሙሉ ስንከታተል የነበረው የሙስና (ወይንም) ጉቦ የመቀበል ወንጀል እና በሕገወጥ መንገድ የተገኘን ገንዘብ ሕጋዊ አስመስሎ የመጠቀም ወንጀል " በሚል ቀርቦባቸዉ ከነበረዉን ክስ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሀዋሳና አከባቢዋ ምድብ ችሎት ዛሬ ሙሉ በሙሉ በነፃ አሰናብቷቸዋል።
በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ ፍርድ ቤት ደግሞ ቀሪ የክስ መዝገቦች እንዳሏቸዉ የጠቀሱት ጠበቃቸው አቶ ገብረመድህን ተክላይ እሳቸዉ ግን ጥብቅናቸዉ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ለነበራቸው ሁለቱ መዝገቦች ብቻ መሆኑን ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በጊዜ ቀጠሮ ላይ ባሉ መዝገቦች ዙሪያ ጉዳዩን ከያዙ ጠበቆች ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ያደረገዉ ሙከራ ለጊዜዉ አልተሳካም።
መረጃዎችን እንዳገኘን ተጨማሪ ዘገባ የምናደርስ ይሆናል።
@tikvahethiopia