ኢትዮዽያ መጓዝ እንደማልችል በአትላንታ የኢትዮዽያ አየር መንገድ ሀላፊ በሆኑት በአቶ ተሾመ ገ/ስላሴ ተነግሮኝ ተመልሻለሁ።
አቶ ልደቱ አያሌው
ወደ ኢትዮዽያ ለመሄድ በኢትዮዽያ አየር መንገድ ትኬት የቆረጥኩት ለዛሬ ስለሆነ ከጧቱ 12 ሰዓት በአትላንታ
ዓለም-አቀፍ አየር ማረፊያ ተገኝቸ ነበር። የአገልግሎት ጊዜው ያላለፈ የኢትዮዽያ ፓስፖርትና የተረጋገጠ የጉዞ ትኬት ይዥ የተገኘሁ ቢሆንም የኢትዮዽያ አየር መንገድ ግን በአሜሪካ የኢትዮዽያ ኤምባሲን አነጋግሬ የተለየ ፈቃድ ካልተሰጠኝ በስተቀር ወደ ኢትዮዽያ መጓዝ እንደማልችል በአትላንታ የኢትዮዽያ አየር መንገድ ሀላፊ በሆኑት በአቶ ተሾመ ገ/ስላሴ ተነግሮኝ ተመልሻለሁ።
በአሸባሪነት ወንጀል ሊከሰኝ እንደሚፈልግና በቁጥጥር ስር እንድውል ከኢንተር-ፖል ጋር ጭምር እየተነጋገረ እንደሆነ ሲገልፅ የነበረው የኢትዮዽያ መንግስት ዛሬ በራሴ ፈቃድ ወደ አገሬ ለመመለስ ስሞክር በእኔ ላይ ህገ-ወጥ ክልከላ ማድረጉ አስገርሞኛል። ምን አልባት እንዲህ አይነቱ ድርጊት በአለም ለመጀመሪያ ጊዜ የተፈፀመ ሊሆን ይችላል። መንግስት እኔን በወንጀለኛነት ከጠረጠረኝ ሊከሰኝና ሊያስረኝ ይችላል እንጅ ወደ አገሬ እንዳልገባ ሊከለክለኝ አይችልም።
አንድን ኢትዮዽያዊ የሆነና የኢትዮዽያ ፓስፖርት የያዘን ዜጋ ወደ አገሩ እንዳይገባ ለመከልከል የሚያስችል ምንም ዓይነት የህግ ማዕቀፍ የለም። ስለሆነም በሌላ አገር አየር መንገድ ትኬት ቆርጨ ሰሞኑን ወደ አገሬ ተመልሸ እንደምሄድ በዚህ አጋጣሚ አሳውቃለሁ።
ከአክብሮት ጋር
ልደቱ አያሌው
@Yenetube @Fikerassefa
አቶ ልደቱ አያሌው
ወደ ኢትዮዽያ ለመሄድ በኢትዮዽያ አየር መንገድ ትኬት የቆረጥኩት ለዛሬ ስለሆነ ከጧቱ 12 ሰዓት በአትላንታ
ዓለም-አቀፍ አየር ማረፊያ ተገኝቸ ነበር። የአገልግሎት ጊዜው ያላለፈ የኢትዮዽያ ፓስፖርትና የተረጋገጠ የጉዞ ትኬት ይዥ የተገኘሁ ቢሆንም የኢትዮዽያ አየር መንገድ ግን በአሜሪካ የኢትዮዽያ ኤምባሲን አነጋግሬ የተለየ ፈቃድ ካልተሰጠኝ በስተቀር ወደ ኢትዮዽያ መጓዝ እንደማልችል በአትላንታ የኢትዮዽያ አየር መንገድ ሀላፊ በሆኑት በአቶ ተሾመ ገ/ስላሴ ተነግሮኝ ተመልሻለሁ።
በአሸባሪነት ወንጀል ሊከሰኝ እንደሚፈልግና በቁጥጥር ስር እንድውል ከኢንተር-ፖል ጋር ጭምር እየተነጋገረ እንደሆነ ሲገልፅ የነበረው የኢትዮዽያ መንግስት ዛሬ በራሴ ፈቃድ ወደ አገሬ ለመመለስ ስሞክር በእኔ ላይ ህገ-ወጥ ክልከላ ማድረጉ አስገርሞኛል። ምን አልባት እንዲህ አይነቱ ድርጊት በአለም ለመጀመሪያ ጊዜ የተፈፀመ ሊሆን ይችላል። መንግስት እኔን በወንጀለኛነት ከጠረጠረኝ ሊከሰኝና ሊያስረኝ ይችላል እንጅ ወደ አገሬ እንዳልገባ ሊከለክለኝ አይችልም።
አንድን ኢትዮዽያዊ የሆነና የኢትዮዽያ ፓስፖርት የያዘን ዜጋ ወደ አገሩ እንዳይገባ ለመከልከል የሚያስችል ምንም ዓይነት የህግ ማዕቀፍ የለም። ስለሆነም በሌላ አገር አየር መንገድ ትኬት ቆርጨ ሰሞኑን ወደ አገሬ ተመልሸ እንደምሄድ በዚህ አጋጣሚ አሳውቃለሁ።
ከአክብሮት ጋር
ልደቱ አያሌው
@Yenetube @Fikerassefa