ዩክሬን ያላትን ማዕድን ለአሜሪካ ለመስጠት ተስማማች
ዩክሬን ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር በዋና ማዕድን ልማት ስምምነት ላይ ደርሳለች ሲሉ የኪዬቭ ከፍተኛ ባለስልጣን ተናግረዋል። ባለሥልጣኑ ምንም ተጨማሪ ዝርዝር መግለጫ ሳይሰጡ "በርካታ ጥሩ ማሻሻያዎች ተስማምተናል እናም እንደ አወንታዊ ውጤትም ተመልክተናል" ብለዋል። የመገናኛ ብዙሃን ዘገባዎች ዋሽንግተን የተፈጥሮ ሀብቱን ከመጠቀም ሊገኝ የሚችለውን 500 ቢሊዮን ዶላር የማግኘት መብትን የመጀመሪያ ጥያቄዎች የተወች ሲሆን ነገር ግን በጦርነት ለተጎዳችው ዩክሬን ጠንካራ የደህንነት ዋስትና የማትሰጥ ይሆናል።
የዩናይትስ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከዩክሬን አቻቸው ቮሎዲሚር ዜለንስኪ በዋሽንግተን በዚህ ሳምንት ስምምነቱን ይፈራረማሉ ብለው እንደሚጠብቁ ስማቸው ያልተገለፀ የዩክሬን ባለስልጣን ተናግረዋል ።
ስምምነት ላይ መድረሱን ሳያረጋግጡ ትራምፕ ማክሰኞ እለት እንደተናገሩት ለስምምነቱ ምላሽ ዩክሬን "የመዋጋት መብት" ታገኛለች ብለዋል። የዩናይትድ ስቴትስ ገንዘብ እና ወታደራዊ መሳሪያዎቿ ባይኖሩ ኖሮ ይህ ጦርነት በአጭር ጊዜ ውስጥ ያበቃ ነበር ሲሉ አክለዋል።
ለዩክሬን የአሜሪካ መሳሪያዎች እና ጥይቶች አቅርቦቶች ይቀጥላሉ ወይ ተብለው ለቀረበላቸው ጥያቄ “ምናልባት ከሩሲያ ጋር ስምምነት ላይ እስክንደርስ ድረስ ድጋፍ ማድረግ አለብን፣ ስምምነቱ ካልተደረሰ ግን ይቀጥላል” ብለዋል። ማንኛውንም የሰላም ስምምነት ተከትሎ በዩክሬን ውስጥ “አንዳንድ የሰላም ማስከበር ዓይነቶች” እንደሚያስፈልግ ትራምፕ አክለው ተናግረዋል።
ባለፈው ሳምንት ትራምፕ ዜለንስኪን “አምባገነን” ሲሉ የገለፁት ሲሆን ጦርነቱን የጀመረችው ዩክሬን ናት ማለታቸው ይታወሳል። የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት የአሜሪካን የ500 ቢሊዮን ዶላር የማዕድን ሀብት ጥያቄ ውድቅ ካደረጉ በኋላ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ሩሲያ በፈጠረችው የሃሰት የመረጃ ውስጥ እንደሚኖሩ ጠቁመዋል። ትራምፕ ሞስኮ ሙሉ ወረራ ከጀመረች ከሦስት ዓመታት በፊት ጀምሮ ዋሽንግተን ላደረገችው ወታደራዊና ሌሎች ድጋፎች የዩክሬን ማዕድን ለማግኘት ግፊት ሲያደርጉ ቆይተዋል።
በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል
ዩክሬን ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር በዋና ማዕድን ልማት ስምምነት ላይ ደርሳለች ሲሉ የኪዬቭ ከፍተኛ ባለስልጣን ተናግረዋል። ባለሥልጣኑ ምንም ተጨማሪ ዝርዝር መግለጫ ሳይሰጡ "በርካታ ጥሩ ማሻሻያዎች ተስማምተናል እናም እንደ አወንታዊ ውጤትም ተመልክተናል" ብለዋል። የመገናኛ ብዙሃን ዘገባዎች ዋሽንግተን የተፈጥሮ ሀብቱን ከመጠቀም ሊገኝ የሚችለውን 500 ቢሊዮን ዶላር የማግኘት መብትን የመጀመሪያ ጥያቄዎች የተወች ሲሆን ነገር ግን በጦርነት ለተጎዳችው ዩክሬን ጠንካራ የደህንነት ዋስትና የማትሰጥ ይሆናል።
የዩናይትስ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከዩክሬን አቻቸው ቮሎዲሚር ዜለንስኪ በዋሽንግተን በዚህ ሳምንት ስምምነቱን ይፈራረማሉ ብለው እንደሚጠብቁ ስማቸው ያልተገለፀ የዩክሬን ባለስልጣን ተናግረዋል ።
ስምምነት ላይ መድረሱን ሳያረጋግጡ ትራምፕ ማክሰኞ እለት እንደተናገሩት ለስምምነቱ ምላሽ ዩክሬን "የመዋጋት መብት" ታገኛለች ብለዋል። የዩናይትድ ስቴትስ ገንዘብ እና ወታደራዊ መሳሪያዎቿ ባይኖሩ ኖሮ ይህ ጦርነት በአጭር ጊዜ ውስጥ ያበቃ ነበር ሲሉ አክለዋል።
ለዩክሬን የአሜሪካ መሳሪያዎች እና ጥይቶች አቅርቦቶች ይቀጥላሉ ወይ ተብለው ለቀረበላቸው ጥያቄ “ምናልባት ከሩሲያ ጋር ስምምነት ላይ እስክንደርስ ድረስ ድጋፍ ማድረግ አለብን፣ ስምምነቱ ካልተደረሰ ግን ይቀጥላል” ብለዋል። ማንኛውንም የሰላም ስምምነት ተከትሎ በዩክሬን ውስጥ “አንዳንድ የሰላም ማስከበር ዓይነቶች” እንደሚያስፈልግ ትራምፕ አክለው ተናግረዋል።
ባለፈው ሳምንት ትራምፕ ዜለንስኪን “አምባገነን” ሲሉ የገለፁት ሲሆን ጦርነቱን የጀመረችው ዩክሬን ናት ማለታቸው ይታወሳል። የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት የአሜሪካን የ500 ቢሊዮን ዶላር የማዕድን ሀብት ጥያቄ ውድቅ ካደረጉ በኋላ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ሩሲያ በፈጠረችው የሃሰት የመረጃ ውስጥ እንደሚኖሩ ጠቁመዋል። ትራምፕ ሞስኮ ሙሉ ወረራ ከጀመረች ከሦስት ዓመታት በፊት ጀምሮ ዋሽንግተን ላደረገችው ወታደራዊና ሌሎች ድጋፎች የዩክሬን ማዕድን ለማግኘት ግፊት ሲያደርጉ ቆይተዋል።
በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል