በኢትዮጵያ እና ኬንያ ድንበር በተፈጠረው ግጭት ከ13 በላይ ኢትዮጵያዊያን ዜጎች ህይወት አለፈ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዳሰነች እና በሰሜን ኬንያ ቱርካና የድንበር አከባቢ የኢትዮጵያን ድንበር ዘልቀው የገቡ የቱርካና ታጣቂ የሚልሻ አባላት አርብቶ አደሮች ባደረሱት ጥቃት የ13 ንፁሀን ዜጎች ህይወት ሲያልፍ 3 ሰዎች በከፍተኛ የህክምና ክትትል ላይ እንደሚገኙ የደቡብ ኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሚሽን ህዝብ ግንኙነት እና ገጽታ ግንባታ ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር አሸናፊ ኃይሌ ለብስራት ሬዲዮ ቴሌቪዥን ተናግረዋል።
"ከየካቲት 12 ቀን 2017 ከቀኑ 8 ሰዓት ጀምሮ የኢትዮጵያን ድንበር ዘልቀው የገቡ የተደራጁ ታጣቂ የሚልሻ አባላት ተከታታይነት ባለው ሁኔታ በተለያዩ አካባቢዎች ባደረሱት ጥቃት በአከባቢው ከፍተኛ ውድመት ደርሷል"።
ይህንን ተከትሎ የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ኢትዮጵያ እና ኬንያ በሚዋሰኑበት የድንበር አከባቢ በንፁሀን ኢትዮጵያዊያን ዜጎች ላይ የደረሰው የህይወት መጥፋትና የንብረት ዘረፋን አስመልክቶ ከአካካቢው ማህበረሰብ ጋር ተወያይተዋል።
በተደጋጋሚ ድንበር ዘልቀው የሚገቡ ታጣቂዎች በሚያደርሱት ጉዳት ለከፍተኛ ችግር መጋለጣወን ነዋሪዎች የገለፁ ሲሆን መንግሥት በድንበር አከባቢ ዘላቂ ሠላምን ለማስፈን ከጎረቤት ሀገር ኬንያ መንግሥት ጋር ሊሰራ ይገባል ሲሉ መናገራቸውን ኮማንደር አሸናፊ ኃይሌ ለብስራት ሬዲዮ ቴሌቪዥን ተናግረዋል።
በሳምራዊት ስዩም
#ዳጉ_ጆርናል
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዳሰነች እና በሰሜን ኬንያ ቱርካና የድንበር አከባቢ የኢትዮጵያን ድንበር ዘልቀው የገቡ የቱርካና ታጣቂ የሚልሻ አባላት አርብቶ አደሮች ባደረሱት ጥቃት የ13 ንፁሀን ዜጎች ህይወት ሲያልፍ 3 ሰዎች በከፍተኛ የህክምና ክትትል ላይ እንደሚገኙ የደቡብ ኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሚሽን ህዝብ ግንኙነት እና ገጽታ ግንባታ ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር አሸናፊ ኃይሌ ለብስራት ሬዲዮ ቴሌቪዥን ተናግረዋል።
"ከየካቲት 12 ቀን 2017 ከቀኑ 8 ሰዓት ጀምሮ የኢትዮጵያን ድንበር ዘልቀው የገቡ የተደራጁ ታጣቂ የሚልሻ አባላት ተከታታይነት ባለው ሁኔታ በተለያዩ አካባቢዎች ባደረሱት ጥቃት በአከባቢው ከፍተኛ ውድመት ደርሷል"።
ይህንን ተከትሎ የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ኢትዮጵያ እና ኬንያ በሚዋሰኑበት የድንበር አከባቢ በንፁሀን ኢትዮጵያዊያን ዜጎች ላይ የደረሰው የህይወት መጥፋትና የንብረት ዘረፋን አስመልክቶ ከአካካቢው ማህበረሰብ ጋር ተወያይተዋል።
በተደጋጋሚ ድንበር ዘልቀው የሚገቡ ታጣቂዎች በሚያደርሱት ጉዳት ለከፍተኛ ችግር መጋለጣወን ነዋሪዎች የገለፁ ሲሆን መንግሥት በድንበር አከባቢ ዘላቂ ሠላምን ለማስፈን ከጎረቤት ሀገር ኬንያ መንግሥት ጋር ሊሰራ ይገባል ሲሉ መናገራቸውን ኮማንደር አሸናፊ ኃይሌ ለብስራት ሬዲዮ ቴሌቪዥን ተናግረዋል።
በሳምራዊት ስዩም
#ዳጉ_ጆርናል