በአውስትራሊያ አንዲት ነርስ ለእስራኤላውያን ታካሚዎች ህክምና እንደማትሰጥ በመናገሯና በመዛቷ ክስ ተመሰረተባት
በአውስትራሊያ የምትኖር አንዲት ነርስ የሆስፒታሉ ሰራተኞች ለእስራኤል ታማሚዎች ህክምና እንዳይሰጡ እና የግድያ ዛቻ ስትፈፅም የሚያሳይ ቪዲዮ መሰራጨቱን ተከትሎ ክስ ተመስርቶባታል። የኒው ሳውዝ ዌልስ ፖሊስ ረቡዕ ዕለት እንዳስታወቀው የ26 ዓመቷን ሴት በሶስት ወንጀሎች ክስ እንደተመሰረተባት ይፋ አድርጓል።
የኒው ሳውዝ ዌልስ ፖሊስ ኮሚሽነር ካረን ዌብ እንዳሉት ሴትየዋ ሳራ አቡ ሌብዴህ የምትባል ሲሆን አውስትራሊያን ለቅቃ እንዳትወጣ እና ማህበራዊ ትስስር ገጾችን እንዳትጠቀም ተከልክላለች። ዌብ እንደተናገሩይ ሴትየዋ በመጋቢት 19 በሲድኒ ፍርድ ቤት ትቀርባለች ብለዋል። ይህ እርምጃ የተወሰደው በሲድኒ ሆስፒታል ውስጥ የሚገኙ ሁለት የእስራኤል ታማሚዎችን ለመጉዳት ስትፎክር የሚያሳይ ምስል በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በመሰራጨቱ የተነሳ ሲሆን ሰፊ ውግዘት አስከትሏል።
በእስራኤላዊው የይዘት ፈጣሪ ማክስ ቬፈር በተጋራ የቪዲዮ ውይይት ላይ አቡ ሌብዴህ ህክምና የሚፈልጉ እስራኤላውያንን እንደማታከም እና "እንደምትገድላቸው ስትናገር ትታያለች። በቪዲዮው ላፕ በተጨማሪም አንድ ወንድ የሆስፒታል ባልደረባ ብዙ እስራኤላውያን ታካሚዎችን ወደ ሲኦል እንደላከ ሲናገር ይታያል። በሀገር ውስጥ በወጡ ዘገባዎች አህመድ ረሻድ ናዲር የተባለው ግለሰብ በድርጊቱ ክስ አልተመሰረተበትም።
የአውስትራሊያው ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኔዝ “አስጸያፊ ፣ አሳፋሪ ” በማለት አውግዘዋል። የጤና ባለሥልጣናት ሁለቱ የሆስፒታል ሠራተኞች በጤና አጠባበቅ ውስጥ “በማንኛውም ሁኔታ” እንዳይሠሩ አግደዋል ። የጤና ባለሥልጣናቱ እስራኤላውያን የሆኑ ሕመምተኞች ጉዳት እንደደረሰባቸው የሚያሳይ ምንም ማስረጃ እንዳላገኙ ተናግረዋል።
በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል
በአውስትራሊያ የምትኖር አንዲት ነርስ የሆስፒታሉ ሰራተኞች ለእስራኤል ታማሚዎች ህክምና እንዳይሰጡ እና የግድያ ዛቻ ስትፈፅም የሚያሳይ ቪዲዮ መሰራጨቱን ተከትሎ ክስ ተመስርቶባታል። የኒው ሳውዝ ዌልስ ፖሊስ ረቡዕ ዕለት እንዳስታወቀው የ26 ዓመቷን ሴት በሶስት ወንጀሎች ክስ እንደተመሰረተባት ይፋ አድርጓል።
የኒው ሳውዝ ዌልስ ፖሊስ ኮሚሽነር ካረን ዌብ እንዳሉት ሴትየዋ ሳራ አቡ ሌብዴህ የምትባል ሲሆን አውስትራሊያን ለቅቃ እንዳትወጣ እና ማህበራዊ ትስስር ገጾችን እንዳትጠቀም ተከልክላለች። ዌብ እንደተናገሩይ ሴትየዋ በመጋቢት 19 በሲድኒ ፍርድ ቤት ትቀርባለች ብለዋል። ይህ እርምጃ የተወሰደው በሲድኒ ሆስፒታል ውስጥ የሚገኙ ሁለት የእስራኤል ታማሚዎችን ለመጉዳት ስትፎክር የሚያሳይ ምስል በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በመሰራጨቱ የተነሳ ሲሆን ሰፊ ውግዘት አስከትሏል።
በእስራኤላዊው የይዘት ፈጣሪ ማክስ ቬፈር በተጋራ የቪዲዮ ውይይት ላይ አቡ ሌብዴህ ህክምና የሚፈልጉ እስራኤላውያንን እንደማታከም እና "እንደምትገድላቸው ስትናገር ትታያለች። በቪዲዮው ላፕ በተጨማሪም አንድ ወንድ የሆስፒታል ባልደረባ ብዙ እስራኤላውያን ታካሚዎችን ወደ ሲኦል እንደላከ ሲናገር ይታያል። በሀገር ውስጥ በወጡ ዘገባዎች አህመድ ረሻድ ናዲር የተባለው ግለሰብ በድርጊቱ ክስ አልተመሰረተበትም።
የአውስትራሊያው ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኔዝ “አስጸያፊ ፣ አሳፋሪ ” በማለት አውግዘዋል። የጤና ባለሥልጣናት ሁለቱ የሆስፒታል ሠራተኞች በጤና አጠባበቅ ውስጥ “በማንኛውም ሁኔታ” እንዳይሠሩ አግደዋል ። የጤና ባለሥልጣናቱ እስራኤላውያን የሆኑ ሕመምተኞች ጉዳት እንደደረሰባቸው የሚያሳይ ምንም ማስረጃ እንዳላገኙ ተናግረዋል።
በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል