Фильтр публикаций


ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ በደሴ እና በኮምቦልቻ ከተሞች የልማት ሥራዎችን ይጎበኛሉ።

ባሕር ዳር: መጋቢት 02/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ርእሰ መሥተዳደር አረጋ ከበደ እና ምክትል ርእሰ አብዱ ሁሴን (ዶ.ር) የልማት ሥራዎችን ለመጎብኘት ኮምቦልቻ ከተማ ገብተዋል።

ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ እና ምክትል ርእሰ መሥተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ.ር) ኮምቦልቻ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የደቡብ ወሎ ዞን፣ የደሴ ከተማ አሥተዳደር እና የኮምቦልቻ ከተማ አሥተዳደር መሪዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል።

ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎቹ በደሴ በሚኖራቸው ቆይታ የልማት ሥራዎችን ይጎበኛሉ ተብሏል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!


https://www.ameco.et/72071/
ሃይማኖትን ሽፋን አድርገው አብሮነትን ሊሸረሽሩ የሚችሉ ግጭት ቀስቃሽ መልዕክቶችን የሚያስተላልፉ አካላትን በጽኑ እንደሚያወግዝ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ገለጸ።


https://www.ameco.et/72068/
“ባለፉት ሰባት ዓመታት የክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር የኮሚኒኬሽን ዘዴ ለየት ባለ መንገድ ግልጽነት እና ተደራሽነትን በማለም የተከናወነ ነው” ጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤት


አሚኮ እለታዊ የምንዛሬ መረጃ
መጋቢት 2/2017 ዓ.ም


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
ጥቂት ስለ ለሚ ናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ !
👉በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን እንሳሮ ወረዳ የሚገኘው የለሚ ናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ ከ1 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ጊዜያዊ እና ቋሚ የሥራ እድል ፈጥሯል
👉ፋብሪካው ወደ ሥራ ከገባበት ጊዜ ጀምሮ እስካሁን 7 ሚሊየን ኩንታል ሲሚንቶ ለገበያ አቅርቧል
👉አሁን ላይ በቀን 100 ሺህ ኩንታል ሲሚንቶ እያመረተ ነው
👉በኢትዮጵያ 33 በመቶ በላይ የሚሆነውን የሲሚንቶ አቅርቦት መሸፈን ችሏል
👉ለሚ ናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ በ2017 በጀት ዓመት የጥንካሬ ደረጃዎችን ካሳኩ አቻ ኢትዮጵያዊያን ምርቶች በጥራት ተሸላሚ መሆን መቻሉም ተመላክቷል፡፡
👉በአማራ ክልል ግዙፍ ፋብሪካዎች ስኬታማ መሆን እንደሚችሉ ለሚ ናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ ትልቅ ማሳያ ነው።


#አንኳር
"የዘንድሮውን የሴቶች ቀን ከአዳራሽ ውይይት እና ቀኑን አስቦ ከመዋል ባለፈ የሴቶችን ተጠቃሚነት እና ተሳታፊነት ባረጋገጠ መልኩ በልዩ ልዩ ኹነቶች በድምቀት ማክበር ተችሏል"
የአማራ ክልል ሴቶች፣ ሕጻናት እና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኀላፊ ብርቱካን ሲሳይ


አሚኮ እለታዊ የምንዛሬ መረጃ
መጋቢት 1/2017 ዓ.ም


የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) መልእክት!

ዛሬ የስካይ ዊን ኤሮኖቲክስ ኢንደስትሪን መርቀናል።

ከጥቂት ዓመታት በፊት በሀገር ውስጥ ድሮን ስለማምረት ማሰብ የማይታሰብ ነበር። ብዙ አይነት ችሎታ ያላቸው ድሮኖችን በራሳችን ባለሞያዎች ዲዛይን አድርጎ የማምረት አቅም ትልቅ የታሪክ እጥፋት ነው። ይኽን እድገት ለማዝለቅ ቀጣይነት ባለው የምርምር ሥራ ላይ፣ ገበያ በማስፋት ተግባር ላይ እና በሀገር ውስጥ የስማርት ሴንሰር ቴክኖሎጂዎችን በማምረት ላይ መሥራት ይገባናል።

እንደዚህ እና እንደሆሚቾ የተተኳሽ ኢንጂነሪንግ ፋብሪካ ያሉትን አቅሞቻችንን የምናሳድገው ግጭትን ለማቀጣጠል አይደለም። ግጭትን ለማስቀረት እንጂ። ግጭትን በሚፈልጉ ተዋንያን ፊት ግጭትን ለማስቀረት የሚችል አቅም በመፍጠር ሰላም እና መረጋጋትን ለማፅናት ነው ፍላጎታችን።


ጠንካራ ሀገር የመገንባት ግብን መሠረት በማድረግ ውጤታማ ሥራዎች መሠራታቸውን ብልጽግና ፓርቲ አስታወቀ።

ለሦስት ተከታታይ ቀናት ሲካሄድ የቆየው የብልጽግና ፓርቲ የ6 ወራት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ ተጠናቅቋል።

ስኬቶችን ለማስቀጠል፣ ክፍተቶችን ለመሙላት እና ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉም ተጠቁሟል።

ከብልጽግና ፓርቲ የተገኘው መረጃ እንደሚያመላክተው የኑሮ ውድነትን ለመቀነስ፣ ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራን ለማሳደግ እና ከተረጂነት መላቀቅ ሀገራዊ ግብን ለማሳካት የተሠሩ ውጤታማነት ሥራዎችን ማስቀጠል እንደሚገባ መግባባት ላይ ተደርሷል።


https://www.ameco.et/72026/
ጠንካራ ሀገር የመገንባት ግብን መሠረት በማድረግ ውጤታማ ሥራዎች መከናወናቸውን ብልጽግና ፓርቲ አስታወቀ።


#አንኳር
"የኢትዮጵያ ሴቶች ለሀገራቸው ነፃነት፣ የኢኮኖሚ ዕድገት፤ ማኅበራዊ እሴቶችና ባሕሎችን ለማፅናት ያበረከቱት አስተዋፅዖ የላቀ ነው፤ እንቅፋቶችን እና ጎታች እሳቤዎችን በመጣል፣ በመላ አቅማቸው የሀገራችን የመዘመን መንገድ ዋነኛ መሪና ተዋናይ መኾናቸው እሙን ነው"
ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ


https://www.ameco.et/71998/
የሕዝብ ውክልናን ለመወጣት የሚደረጉ ጥረቶች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ አሳሰቡ።


ወሎ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን እያስመረቀ ነው።
ደሴ: የካቲት 29/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ወሎ ዩኒቨርሲቲ ለ16ኛ ዙር በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 1 ሺህ 320 ተማሪዎች እያስመረቀ ነው።
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!


በሚሊዮኖች የምትጎበኘው ደብረ ምጥማቅ ጻድቃኔ ማርያም

በአማራ ክልል በሰሜን ሸዋ ዞን በሞጃና ወደራ ወረዳ የምትገኘው የጻድቃኔ ማርያም መካነ ቅዱሳን ገዳም በሰላ ድንጋይ ከተማ አቅራቢያ ትገኛለች። ቦታው ከክልሉ ርእሰ ከተማ ባሕር ዳር 767 ኪሎ ሜትር፣ ከአዲስ አበባ 202 ኪሎ ሜትር እና ከዞኑ ርእሰ ከተማ ደብረ ብርሃን 72 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል።

ይህ ቅዱስ ሥፍራ በአፄ ዘርዓያዕቆብ እንደተቆረቆረ ሊቃውንቱ ይናገራሉ ። ጽላቷ ወደቦታው ስትመጣ ንጉሠ ነገሥቱ በእልልታና በደስታ ተቀብለው በዘመኑ ለነበሩት ካህናትና ዲያቆናት አስረከቧቸው፡፡
ቀጥሎም አጼ ዘርዓ ያዕቆብ ጅባት ከተባለው ከተማ ወደ እንጦጦ አምጥተው ለብዙ ጊዜ አስቀምጠዋታል፡፡ እንደገናም ከእንጦጦ አንስተው ወደ ደብረ ብርሃን አመጧት።
ከዚያም አሁን ወዳለችበት አካባቢ ወደ ሰላ ድንጋይ ሞሊያ በተባለው ከፍተኛ ቦታ ለብዙ ዓመታት መቆየቷን የገዳሟ መረጃ ይጠቁማል።

https://ameco.et/tourism/953/


#አንኳር
"ማርች 8 ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን በተግባር ስናከብር፤ የሴቶችን ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና ፖለቲካዊ ተሳታፊነታቸውንና ተጠቃሚነታቸውን በሚያሳድግ አግባብ መኾን አለበት"
ወይዘሮ ብርቱካን ሲሳይ
የአማራ ክልል ሴቶች፣ ሕፃናት እና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ


ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን አስመልክተው ያስተላለፉት መልዕክት!

"እንኳን ለዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን፣ ማርች 8 አደረሰን! የኢትዮጵያ ሴቶች ለሀገራቸው ነፃነት፣ የኢኮኖሚ ዕድገት: ማኅበራዊ እሴቶችና ባሕሎችን ለማፅናት ያበረከቱት አስተዋፅኦ የላቀ ነው፤ እንቅፋቶችንና ጎታች እሳቤዎችን በመጣል፣ በመላ አቅማቸው የሀገራችን የመዘመን መንገድ ዋነኛ መሪና ተዋናይ መሆናቸው እሙን ነው"


የአማራ ክልል የሕዝብ ተወካዮች ከክልሉ ከፍተኛ መሪዎች ጋር እየመከሩ ነው።

ባሕር ዳር: የካቲት 29/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የአማራ ክልል ምክር ቤት አባላት የመራጭ ተመራጭ የውይይት መድረክ ሲያካሂዱ ቆይተዋል። ዛሬ ደግሞ ከሕዝብ በተነሱ የልማት እና የመልካም አሥተዳደር ጥያቄዎች ላይ ከአማራ ክልል አመራሮች ጋር በባሕር ዳር ከተማ እየተወያዩ ነው።

በውይይቱ ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ፣ የአማራ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ፣ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች፣ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የመንግሥት ረዳት ተጠሪ መሠረት ኃይሌን እና በተወካዮች ምክር ቤት የአማራ ክልል ተመራጮች ተገኝተዋል።

በውይይቱ ከሕዝብ የተነሱ ጥያቄዎች ላይ በመወያየት ልማት በሚፋጠንበት፣ በክልሉ ያለው የሰላም እጦት በዘላቂነት በሚፈታበት እና ተዛማጅ ጉዳዮች ላይ እንደሚመክሩ ይጠበቃል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን


#ማርች 8
ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን በዓለም 114ኛ በሀገራችን ለ49ኛ ጊዜ "ፈጣን እና ቀጣይነት ያለው ለውጥ በሴቶች ተሳትፎ ይረጋገጣል" በሚል መሪ መልእክት እየተከበረ ነው።

Показано 18 последних публикаций.