የአውሮፓ ሀገራት መሪዎች ለዩክሬን ያላቸዉን ድጋፍ እየገለፁ ነዉ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮለድሚር ዘለንስኪ ከዶናልድ ትራምፕ ጋር በዋይት ሀውስ የነበራቸዉን ፍጥጫ ተከትሎ አዉሮፓዉያኑ ከዩክሬን ጎን መሠለፋቸዉን ተናግረዋል።
የጀርመን ፣ የፈረንሳይ ፣ የስፔን ፣ የፖላንድ እና የኔዘርላንድስ መሪዎች ዩክሬንን የሚደግፉ የማህበራዊ ሚዲያ መልዕክቶችን ካስተላለፉት መካከል ሲሆኑ ዘለንስኪም ለእያንዳንዳቸው
ድጋፍ በቀጥታ የምስጋና ምላሽ ሰጥተዋል።
የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ከኋይት ሀውስ መልስ በእንግሊዙ ጠቅላይ ሚኒስትር ኪር ስታርመር በተዘጋጀው ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ለንደን መግባታቸውም ተገልጿል።
ለዩክሬን ድጋፋቸዉን እያሳዩ ከሚገኙት መካከል የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን "አጥቂ ሩሲያ፤ ተጎጂ ዩክሬን ዩክሬንን መርዳት እና በሩሲያ ላይ ከሶስት አመት በፊት ማዕቀብ መጣላችን ትክክል ነበር" ማለታቸዉ ተሰምቷል።
ለዩክሬን የድጋፍ መልእክቶች ከላኩ ሀገራት ኦስትሪያ፣ ቤልጂየም፣ ክሮሺያ፣ ዴንማርክ፣ ኢስቶኒያ፣ ፊንላንድ፣ አየርላንድ፣ ላትቪያ፣ ሊትዌኒያ፣ ሉክሰምበርግ፣ ሞልዶቫ፣ ሮማኒያ፣ ስዊድን እና ስሎቬንያ ተጠቃሽ ናቸዉ።
በዛሬዉ ዕለት የኔቶ ዋና ፀሃፊ ማርክ ሩት ከዋይት ሀውስ ስብሰባ በኋላ ከዘለንስኪ ጋር ሁለት ጊዜ መነጋገራቸውን ለቢቢሲ ተናግረዋል። ዘገባዉ የቢቢሲ ነዉ።
በ- ሊያ ክብሮም
@Ethionews433 @Ethionews433
።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮለድሚር ዘለንስኪ ከዶናልድ ትራምፕ ጋር በዋይት ሀውስ የነበራቸዉን ፍጥጫ ተከትሎ አዉሮፓዉያኑ ከዩክሬን ጎን መሠለፋቸዉን ተናግረዋል።
የጀርመን ፣ የፈረንሳይ ፣ የስፔን ፣ የፖላንድ እና የኔዘርላንድስ መሪዎች ዩክሬንን የሚደግፉ የማህበራዊ ሚዲያ መልዕክቶችን ካስተላለፉት መካከል ሲሆኑ ዘለንስኪም ለእያንዳንዳቸው
ድጋፍ በቀጥታ የምስጋና ምላሽ ሰጥተዋል።
የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ከኋይት ሀውስ መልስ በእንግሊዙ ጠቅላይ ሚኒስትር ኪር ስታርመር በተዘጋጀው ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ለንደን መግባታቸውም ተገልጿል።
ለዩክሬን ድጋፋቸዉን እያሳዩ ከሚገኙት መካከል የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን "አጥቂ ሩሲያ፤ ተጎጂ ዩክሬን ዩክሬንን መርዳት እና በሩሲያ ላይ ከሶስት አመት በፊት ማዕቀብ መጣላችን ትክክል ነበር" ማለታቸዉ ተሰምቷል።
ለዩክሬን የድጋፍ መልእክቶች ከላኩ ሀገራት ኦስትሪያ፣ ቤልጂየም፣ ክሮሺያ፣ ዴንማርክ፣ ኢስቶኒያ፣ ፊንላንድ፣ አየርላንድ፣ ላትቪያ፣ ሊትዌኒያ፣ ሉክሰምበርግ፣ ሞልዶቫ፣ ሮማኒያ፣ ስዊድን እና ስሎቬንያ ተጠቃሽ ናቸዉ።
በዛሬዉ ዕለት የኔቶ ዋና ፀሃፊ ማርክ ሩት ከዋይት ሀውስ ስብሰባ በኋላ ከዘለንስኪ ጋር ሁለት ጊዜ መነጋገራቸውን ለቢቢሲ ተናግረዋል። ዘገባዉ የቢቢሲ ነዉ።
በ- ሊያ ክብሮም
@Ethionews433 @Ethionews433