ዩናይትድ ስቴትስ የንግድ ጦርነቱን ከቀጠለች ቻይና እስከ መራሩ ፍጻሜ ድረስ ለመታገል ቃል ገባች
የቻይና የገንዘብ ሚኒስቴር በአሜሪካ የታጣለውን ታሪፍ የአፀፋ ምላሽ በመስጠት ከማርች 10 ጀምሮ ተግባራዊ የሚሆን ታሪፍ ከአሜሪካ በሚመጡ ምርቶች ላይ እንደሚጣል አረጋግጧል ። በመግለጫው ውስጥ እንደተገለፀው በዶሮ፣ ስንዴ፣ በቆሎ እና ጥጥ ላይ 15 በመቶ ታሪፍ ይጣልበታል። በማሽላ፣ በአኩሪ አተር፣ በአሳማ ሥጋ፣ በበሬ ሥጋ፣ በውሃ ምርቶች፣ ፍራፍሬዎች፣ አትክልቶች እና የወተት ተዋጽኦዎች ላይ ደግሜ የ10 በመቶ ታሪፍ ይጣልበታል።
መግለጫው አክሎም “ከመጋቢት 10 ቀን 2025 በፊት ከመነሻ ቦታ የተላኩ እና ከመጋቢት 10 ቀን 2025 እስከ ኤፕሪል 12 ቀን 2025 የገቡ ዕቃዎች በዚህ ማስታወቂያ ላይ በተደነገገው ተጨማሪ ታሪፍ አይገደዱም” ሲል ገልጿል። ዩናይትስ ስቴት የንግድ ጦርነት ድርጊቷን ከቀጠለች እስከ “መራር መጨረሻ” ድረስ እንደምትታገል ቻይና ተናግራለች። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ሊን ጂያን ማክሰኞ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ዩናይትድ ስቴትስ የታሪፍ ጦርነት፣ የንግድ ጦርነት ወይም ሌላ ዓይነት ጦርነት ማካሄድ ከቀጠለች የቻይናው ወገን እስከ መጨረሻው ድረስ ይዋጋቸዋል ሲሉ ተደምጠዋል።
በተለያዩ የአሜሪካ የግብርና እና የምግብ ምርቶች ላይ እስከ 15 በመቶ የሚደርስ ታሪፍ የሚያጠቃልለው የቤጂንግ አጸፋዊ እርምጃ የቻይናን ጥቅም ለማስጠበቅ ነው ተብሏል። ሊን በተቻለ ፍጥነት ዋሽንግተን ከቤጂንግ ጋር ወደ ውይይት እንድትመለስ አሳስበዋል። የትራምፕ አስተዳደር ለረጅም ጊዜ ስጋት ፈጥሮ የነበረው በካናዳ እና በሜክሲኮ ላይ ይጣላል የተባለው የ25 በመቶ ታሪፍ በዋሽንግተን ዲሲ ሰዓት አቆጣጠር መሰረት እኩለ ሌሊት ላይ ተጀምሯል። በተመሳሳይ በቻይና ምርቶች ላይ 10 በመቶ ቀረጥ ተጥሏል።ቻይና እና ካናዳ የአፀፋ ምላሽ ሰጥተዋል።
በቻይና መንግስት ስር የሚተዳደረው ግሎባል ታይምስ ጋዜጣ ቤጂንግ የአሜሪካን የግብርና እና የምግብ ምርቶች ላይ ያነጣጠረ የመከላከያ እርምጃዋ መሆኗን ዘግቧል። ቻይና እ.ኤ.አ. በ2018 ከአሜሪካ በሚመጡ አኩሪ አተር ፣በሬ ፣አሳማ ፣ስንዴ እና በቆሎ ላይ እስከ 25 በመቶ የሚደርስ ታሪፍ ብትጥልም ለአሜሪካ የግብርና ምርቶች ትልቁ ገበያ ሆና ቆይታለች። በዓለም ከፍተኛ ኢኮኖሚዎች መካከል ሁሉን አቀፍ የንግድ ጦርነት ሊጀመር እንደሚችል የዘርፉ ባለሙያዎች ስጋታቸውን ገልፀዋል።
በስምኦን ደረጄ
@Ethionews433 @Ethionews433
የቻይና የገንዘብ ሚኒስቴር በአሜሪካ የታጣለውን ታሪፍ የአፀፋ ምላሽ በመስጠት ከማርች 10 ጀምሮ ተግባራዊ የሚሆን ታሪፍ ከአሜሪካ በሚመጡ ምርቶች ላይ እንደሚጣል አረጋግጧል ። በመግለጫው ውስጥ እንደተገለፀው በዶሮ፣ ስንዴ፣ በቆሎ እና ጥጥ ላይ 15 በመቶ ታሪፍ ይጣልበታል። በማሽላ፣ በአኩሪ አተር፣ በአሳማ ሥጋ፣ በበሬ ሥጋ፣ በውሃ ምርቶች፣ ፍራፍሬዎች፣ አትክልቶች እና የወተት ተዋጽኦዎች ላይ ደግሜ የ10 በመቶ ታሪፍ ይጣልበታል።
መግለጫው አክሎም “ከመጋቢት 10 ቀን 2025 በፊት ከመነሻ ቦታ የተላኩ እና ከመጋቢት 10 ቀን 2025 እስከ ኤፕሪል 12 ቀን 2025 የገቡ ዕቃዎች በዚህ ማስታወቂያ ላይ በተደነገገው ተጨማሪ ታሪፍ አይገደዱም” ሲል ገልጿል። ዩናይትስ ስቴት የንግድ ጦርነት ድርጊቷን ከቀጠለች እስከ “መራር መጨረሻ” ድረስ እንደምትታገል ቻይና ተናግራለች። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ሊን ጂያን ማክሰኞ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ዩናይትድ ስቴትስ የታሪፍ ጦርነት፣ የንግድ ጦርነት ወይም ሌላ ዓይነት ጦርነት ማካሄድ ከቀጠለች የቻይናው ወገን እስከ መጨረሻው ድረስ ይዋጋቸዋል ሲሉ ተደምጠዋል።
በተለያዩ የአሜሪካ የግብርና እና የምግብ ምርቶች ላይ እስከ 15 በመቶ የሚደርስ ታሪፍ የሚያጠቃልለው የቤጂንግ አጸፋዊ እርምጃ የቻይናን ጥቅም ለማስጠበቅ ነው ተብሏል። ሊን በተቻለ ፍጥነት ዋሽንግተን ከቤጂንግ ጋር ወደ ውይይት እንድትመለስ አሳስበዋል። የትራምፕ አስተዳደር ለረጅም ጊዜ ስጋት ፈጥሮ የነበረው በካናዳ እና በሜክሲኮ ላይ ይጣላል የተባለው የ25 በመቶ ታሪፍ በዋሽንግተን ዲሲ ሰዓት አቆጣጠር መሰረት እኩለ ሌሊት ላይ ተጀምሯል። በተመሳሳይ በቻይና ምርቶች ላይ 10 በመቶ ቀረጥ ተጥሏል።ቻይና እና ካናዳ የአፀፋ ምላሽ ሰጥተዋል።
በቻይና መንግስት ስር የሚተዳደረው ግሎባል ታይምስ ጋዜጣ ቤጂንግ የአሜሪካን የግብርና እና የምግብ ምርቶች ላይ ያነጣጠረ የመከላከያ እርምጃዋ መሆኗን ዘግቧል። ቻይና እ.ኤ.አ. በ2018 ከአሜሪካ በሚመጡ አኩሪ አተር ፣በሬ ፣አሳማ ፣ስንዴ እና በቆሎ ላይ እስከ 25 በመቶ የሚደርስ ታሪፍ ብትጥልም ለአሜሪካ የግብርና ምርቶች ትልቁ ገበያ ሆና ቆይታለች። በዓለም ከፍተኛ ኢኮኖሚዎች መካከል ሁሉን አቀፍ የንግድ ጦርነት ሊጀመር እንደሚችል የዘርፉ ባለሙያዎች ስጋታቸውን ገልፀዋል።
በስምኦን ደረጄ
@Ethionews433 @Ethionews433