Ministry of Revenues of Ethiopia/የገቢዎች ሚኒስቴር


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Экономика


የገቢዎች ሚኒስቴር ኢኮኖሚው የሚያመነጨው ገቢ እንዲሰበስብ ኃላፊነት የተሰጠው የፌዴራል ተቋም ነው፡፡
የጉምሩክ ኮሚሽንን በስሩ ይዞ ተደራጅቷል፡፡

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Экономика
Статистика
Фильтр публикаций


የትራንስፖርት አበል እና የመጓጓዣ ወጪ ከግብር ነፃ የሚደረግበት ሁኔታ

ጥር 26/2017 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)

ከገቢ ግብር ነፃ የተደረጉ ገቢዎች አፈፃጸም መመሪያ ቁጥር 1/2011 መሠረት

👉በስራ ባህሪው ምክኒያት ስራውን ከቦታ ወደቦታ በመዘዋወር የሚያከናውን
ተቀጣሪ በአንድ ወር ጉዞ የሚከፈለው የትራንስፖርት አበል ከገቢ ግብር ነፃ
የሚደረገው ከጠቅላላ የወር ደመወዙ ከአንድ አራተኛ(1/4) ባልበለጠ መጠን ብቻ
ነው፡፡ ይሁንና የተቀጣሪው ጠቅላላ የወር ደመወዝ አንድ አራተኛ ከብር2200
የሚበልጥ ሲሆን ከግብር ነፃ የሚደረገው የትራንስፖርት አበል በማንኛውም ሁኔታ
ከብር 2200 ሊበልጥ አይችልም፡፡

👉 አንድ ተቀጣሪ በስራ ባህሪው ምክኒያት በመዘዋወር ለሚሰራው ስራ ለነዳጅ
ወጪ የሚከፈለው ጥሬ ገንዘብ ለትራንስፖርት አበል እንደተከፈለ ተቆጥሮ ከገቢ
ግብር ነፃ የሚደረገው ከጠቅላላ የወር ደመወዙ ከአንድ አራተኛ(1/4) ባልበለጠ
መጠን ብቻ ነው፡፡ ይሁንና የተቀጣሪው ጠቅላላ የወር ደመወዝ አንድ አራተኛ
ከብር 2200 የሚበልጥ ሲሆን ከግብር ነፃ የሚደረገው የነዳጅ ወጪ በማንኛውም
ሁኔታ ከብር 2200 ሊበልጥ አይችልም፡፡

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ፡- https://shorturl.at/PLgIY




ጥር 23/2017 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)
ቅዳሜ ሙሉ ቀን አገልግሎት እንሰጣለን _________________
ልዩ መለያ ኮድ (Unique QR code) ያለበት የደረሰኝ ህትመት
ለማሳተም ፈቃድ ለወሰዳችሁ እና በመውሰድ ላይ ላላችሁ በሙሉ፡፡

የታክስ ደረሰኝ አጠቃቀም እና አስተዳደር መመሪያን ለማሻሻል
በወጣ መመሪያ ቁጥር 188/2017 መሠረት
ከየካቲት 1 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ልዩ መለያ ኮድ (Unique QR code)
የሌለው ደረሰኝ መጠቀም የማይቻል መሆኑ ይታወቃል ፡፡

በመሆኑም ቅዳሜ የሙሉ ቀን አገልግሎት የምንሰጥ
መሆኑን እየገለጽን የቀሩት ቀናት አጭር
በመሆናቸው ምንም እንቅስቃሴ ያልጀመራችሁ ግብር ከፋዮች
ከወዲሁ የህትመት ፈቃድ እንድትወስዱ እናሳስባለን ፡፡

በገቢዎች ሚኒስቴር የምስራቅ አ/አ/አነ/ግ/ከ/ቅ/ጽ/ቤት


#ማስታወቂያ!

ጥር 23/2017 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)

የገቢዎች ሚኒስቴር የኢፋይሊንግ ሲስተምን ደህንነት ለማሻሻል የተለያዩ የውስጥ ማሻሻያዎችን አድርጓል።
ከዚህ በኋላ ስርዓቱን ለመጠቀም ቀጥታ በሚከተሉት አድራሻዎች ብቻ ይግቡ፡፡

👉 https://etax.mor.gov.et/Login/Login

👉 https://etax.mor.gov.et/

እናመሰግናለን፡፡


የገቢዎች ሚኒስቴር ገቢ ከመሰብሰብ ጎን ለጎን ማኅበራዊ ኃላፊነቱን እየተወጣ ነው

ጥር 23/2017 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)

በገቢዎች ሚኒስቴር ዋናው መስሪያ ቤት የሚገኙ አመራሮችና ሠራተኞች ከጥር 22 እስከ 23/2017 ዓ.ም በፈቃደኝነት ደም ለገሱ፡፡

የደም ልገሳው ከመካሄዱ ቀደም ብሎ ስለ ደም ልገሳ መርሃ ግብር ዓላማ ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራ ተሰርቷል፡፡

ገቢ ከመሰብሰብ ጎን ለጎን ደም በመለገስ የማይተካውን የሰው ሕይወት ለማዳን ማኅበራዊ ኃላፊነትን መወጣት እንሚገባ በገቢዎች ሚኒስቴር የማኅበራዊ ጉዳይ ድጋፍና ክትትል ቡድን መሪ ሀናን ባዲ ገልጸዋል፡፡

በብሄራዊ ደም ባንክ የትምህርት እና ቅስቀሳ ባለሙያ የሆኑት ሲስተር አሰጋሽ ጎሳ በሚተካ ደም የማይተካ የሰው ልጅ ሕይወት ለማዳን የገቢዎች ሚኒስቴር ከብሄራዊ የደም ባንክ ጋር በመሆን ተከታታይነት ባለው መልኩ የደም ልገሳ መርሃ ግበሩ በየሦስት ወሩ እተከናወነ በመሆኑ ምስጋናቸውን ገልጸው ይህ ደም የመለገስ ባህል ወደፊትም ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

በደም ልገሳው የተሳተፉት የዋናው መ/ ቤት አመራሮችና ሠራተኞች ደም በመለገሳቸው መደሰታቸውን ገልጽው ሌሎችም በዚህ በጎ ተግባር እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

በእታገኝ አቦሰጥ
ፎቶ:- የትናየት እናዳያፍሩ


ኮሚሽኑ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያው ስድስት ወራት ውስጥ 203,75 ቢሊዪን ብር ገቢ ሰበሰበ

ጥር 22/2017 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)

የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ክቡር ደበሌ ቃበታ በ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያው 6 ወራት የተከናወኑ ስራዎችን አስመልክቶ ለሚዲያ ባለሞያዎች በዛሬው ዕለት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡

ኮሚሽነር ደበሌ በመግለጫቸው በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያው 6 ወራት ብር 190,9 ቢሊዪን ለመሰብሰብ ታቅዶ ብር 203,75 ቢሊዮን በመሰብሰብ ወይም የዕቅዱን 106,73 በመቶ ማሳካት እንደተቻለ ገልፀዋል፡፡

አፈፃፀሙ ከባለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ106,7 ቢሊዩን ብር ብልጫ ማሳየቱን ተናግረዋል ፡፡
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ፡- https://shorturl.at/XJz32


በገቢዎች ሚኒስቴር የመቐለ ቅርንጫፍ /ጽ/ቤት ለታክስ ህግ ተገዥ ለሆኑ ግብር ከፋዮች የዕውቅናና ሽልማት መርሃ-ግብር አካሄደ

ጥር 22/2017 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)

የመቐለ ቅ/ጽ/ቤት በ2016 በጀት ዓመት ለታክስ ህግ ተገዥ ለሆኑ ታማኝ ግብር ከፋዮች የዕውቅና ሽልማት መርሃ-ግብር አካሂዷል።

በገቢዎች ሚኒስቴር ደረጃ የተሻለ የታክስ ህግ ተገዢነትና የላቀ የገቢ አፈፃፀም እንዲመዘገብ ታማኝ ግብር ከፋዮችን በሀገር አቀፍ ደረጃ ዕውቅ መስጠትና መሸለም ከተጀመረ ስድስት ዓመታት ተቆጥረዋል፡፡

በቅርንጫፍ /ጽ/ቤቱ ደረጃም በ2011 እና በ2012 በጀት ዓመት መርሃ-ግብሩ ከተካሄደ በኋላ ዘንድሮ ለሦስተኛ ጊዜ ለ2016 በጀት ዓመት ታማኝ ግብር ከፋዮች ዕውቅና የመስጠት እና የመሸለም መርሃ-ግብር ተካሂዷል።

በገቢዎች ሚኒስቴር የመቐለ ቅርንጫፍ /ጽ/ቤት ስራ አስኪያጅ አቶ ተኽላይ አብርሃ በተሻለ የህግ ተገዥነታቸውና ባበረከቱት የላቀ የገቢ አስተዋፅኦ ተሸላሚ ለሆኑ የቅርንጫፍ /ጽ/ቤቱ ግብር ከፋዮች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን ስለ መርሃ-ግብሩ ዓላማ አጠር ያለ ማብራሪያ አቅርበዋል።

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ፡- https://shorturl.at/Ls5nM


“The ministry is willing to work with the IMF EAST AFRITAC”
Mr. Fikadu Taddese Head of the Minister's office

January 29/2025 (Ministry Of Revenues)

The ministry of Revenues has discussed with the IMF East Africa Regional Technical Assistance Center.

On the occasion, Mr. Fikadu Taddese, Head of the Minister's office, highlighted that the ministry in charge of leading the revenue sector is engaged in several activities. Among those the use of various technologies is the prime one, aimed to provide an advanced service to the customer.

Read more:- https://shorturl.at/nkQQX





Показано 10 последних публикаций.