የትራንስፖርት አበል እና የመጓጓዣ ወጪ ከግብር ነፃ የሚደረግበት ሁኔታ
ጥር 26/2017 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)
ከገቢ ግብር ነፃ የተደረጉ ገቢዎች አፈፃጸም መመሪያ ቁጥር 1/2011 መሠረት
👉በስራ ባህሪው ምክኒያት ስራውን ከቦታ ወደቦታ በመዘዋወር የሚያከናውን
ተቀጣሪ በአንድ ወር ጉዞ የሚከፈለው የትራንስፖርት አበል ከገቢ ግብር ነፃ
የሚደረገው ከጠቅላላ የወር ደመወዙ ከአንድ አራተኛ(1/4) ባልበለጠ መጠን ብቻ
ነው፡፡ ይሁንና የተቀጣሪው ጠቅላላ የወር ደመወዝ አንድ አራተኛ ከብር2200
የሚበልጥ ሲሆን ከግብር ነፃ የሚደረገው የትራንስፖርት አበል በማንኛውም ሁኔታ
ከብር 2200 ሊበልጥ አይችልም፡፡
👉 አንድ ተቀጣሪ በስራ ባህሪው ምክኒያት በመዘዋወር ለሚሰራው ስራ ለነዳጅ
ወጪ የሚከፈለው ጥሬ ገንዘብ ለትራንስፖርት አበል እንደተከፈለ ተቆጥሮ ከገቢ
ግብር ነፃ የሚደረገው ከጠቅላላ የወር ደመወዙ ከአንድ አራተኛ(1/4) ባልበለጠ
መጠን ብቻ ነው፡፡ ይሁንና የተቀጣሪው ጠቅላላ የወር ደመወዝ አንድ አራተኛ
ከብር 2200 የሚበልጥ ሲሆን ከግብር ነፃ የሚደረገው የነዳጅ ወጪ በማንኛውም
ሁኔታ ከብር 2200 ሊበልጥ አይችልም፡፡
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ፡-
https://shorturl.at/PLgIY